የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የቻይና ባለሀብቶች በልዩ ኢኮኖሚ ዞኑ በኢንቨስትመንት ዘርፍ እንዲሰማሩ በቅንጅት ይሰራል - አምባሳደር ቼን ሃይ

Apr 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2017(ኢዜአ)፦ የቻይና ባለሀብቶች በጅማ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች እንዲሰማሩ ከመንግስት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ ገለጹ።

አምባሳደር ቼን ሃይ የጅማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንን ጎብኝተዋል።

አምባሳደሩ በጅማና አካባቢው በስፋት የሚመረተውን አቮካዶ በግብዓትነት በመጠቀም ወደ አውሮፓና አሜሪካ ገበያዎች የሚልከውን አክሻይ ጀይ ኩባንያ የምርት ሂደትና አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል።

በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ በጅማና አካባቢው ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሃብት ማቀነባበር የሚያስችል መብራት፤ ውሃ እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች መኖራቸውን ከጉብኝቱ መረዳት መቻላቸውን ተናግረዋል።

ቻይናውያን ባለሃብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሰማሩ ከኮርፖሬሽኑ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አመልክተዋል።


የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ ዘርፍ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘመን ጁነዲ በበኩላቸው የቻይና ባለሃብቶች ተሳትፎ ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ነጻ የንግድ ቀጣና ከጊዜ ወደ ጊዜ ይበልጥ እያደገ የመጣና ቀዳሚ መሆኑን ገልጸዋል።

ኮርፖሬሽኑ በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ጋር በኢንቨስትመንት እንዲሁም በሰው ሃብት ልማት፤ በእውቀትና ክህሎት ሽግግር ጭምር ያለውን ትብብር ለማጠናከር በቅርበት እየሰራ ነው ብለዋል።

አያይዘውም ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞንነት በመሸጋገር ሂደት ላይ ያሉ ተጨማሪ የኢንቨስትመንትና በመንግስት እየተወሰዱ ያሉ የኢንቨስትመንት ማበረታቻ የሪፎርም ተግባራትን አንስተዋል።

ቻይናውያን ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉ ምቹ አማራጮችን ተጠቅመው በዘርፉ እንዲሰማሩ ጥሪ ማቅረባቸውን የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026