
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 29/2017(ኢዜአ)፦ የቻይና ባለሀብቶች በጅማ ልዩ ኢኮኖሚ ዞን በተለያዩ የኢንቨስትመንት መስኮች እንዲሰማሩ ከመንግስት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ በኢትዮጵያ የቻይና አምባሳደር ቼን ሃይ ገለጹ።
አምባሳደር ቼን ሃይ የጅማ ልዩ የኢኮኖሚ ዞንን ጎብኝተዋል።
አምባሳደሩ በጅማና አካባቢው በስፋት የሚመረተውን አቮካዶ በግብዓትነት በመጠቀም ወደ አውሮፓና አሜሪካ ገበያዎች የሚልከውን አክሻይ ጀይ ኩባንያ የምርት ሂደትና አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል።
በልዩ የኢኮኖሚ ዞኑ በጅማና አካባቢው ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሃብት ማቀነባበር የሚያስችል መብራት፤ ውሃ እና ሌሎች መሰረተ ልማቶች መኖራቸውን ከጉብኝቱ መረዳት መቻላቸውን ተናግረዋል።
ቻይናውያን ባለሃብቶች በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች እንዲሰማሩ ከኮርፖሬሽኑ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት እንደሚሰራ አመልክተዋል።

የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን የኢንቨስትመንት ፕሮሞሽንና ማርኬቲንግ ዘርፍ ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘመን ጁነዲ በበኩላቸው የቻይና ባለሃብቶች ተሳትፎ ኮርፖሬሽኑ በሚያስተዳድራቸው ልዩ የኢኮኖሚ ዞኖችና ነጻ የንግድ ቀጣና ከጊዜ ወደ ጊዜ ይበልጥ እያደገ የመጣና ቀዳሚ መሆኑን ገልጸዋል።
ኮርፖሬሽኑ በኢትዮጵያ የቻይና ኤምባሲ ጋር በኢንቨስትመንት እንዲሁም በሰው ሃብት ልማት፤ በእውቀትና ክህሎት ሽግግር ጭምር ያለውን ትብብር ለማጠናከር በቅርበት እየሰራ ነው ብለዋል።
አያይዘውም ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ወደ ልዩ ኢኮኖሚ ዞንነት በመሸጋገር ሂደት ላይ ያሉ ተጨማሪ የኢንቨስትመንትና በመንግስት እየተወሰዱ ያሉ የኢንቨስትመንት ማበረታቻ የሪፎርም ተግባራትን አንስተዋል።
ቻይናውያን ባለሀብቶች በኢንዱስትሪ ፓርኮች ያሉ ምቹ አማራጮችን ተጠቅመው በዘርፉ እንዲሰማሩ ጥሪ ማቅረባቸውን የኮርፖሬሽኑ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026