
ነቀምቴ፤ መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ):- በምስራቅ ወለጋ ዞን በየ2017/18 የምርት ዘመን የሚውል ከ230 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በምስራቅ ወለጋ ዞን ግብርና ፅህፈት ቤት የግብርና መካናይዜሽን የግብዓት ፍላጎት እና አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ለሚ አጋ እንዳሉት በየ2017/18 ምርት ዘመኑ 800 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ ነው።
በእስካሁኑ ሂደት 65 ሺህ 378 ኩንታል 'ዳፕ' እና 165 ሺህ ኩንታል 'ዩሪያ' የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል።
እንዲሁም 20 ሺህ ኩንታል ምርጥ ዘር ለማቅረብ የታቅዶ ሲሆን እስካሁን 10 ሺህ 50 ኩንታል ለአርሶ አደሩ መድረሱን ጠቅሰው ያለውን ፍላጎት ለሟሟላት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የስርጭቱ ሂደት ከመልካም አስተዳደር ችግር በጸዳ መልኩ እንዲከናወን ሽያጩ በዲጂታል መንገድ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አስፋው ሀንቢሳ፤ በዞኑ በተለያዩ ኢኒሼቲቮች አመቱን ሙሉ የግብርና ስራ እንዲከናወን ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።
በዚህም የዞኑ አርሶ አደር በምግብ ራሱን ከመቻል ባሻገር ለሀገር ውስጥና እና ለውጪ ገበያ የሚውሉ ምርቶችን ማምረት መጀመሩን ጠቁመዋል።
በዞኑ የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ እንዲቀርብ ከማድረግ ባሻገር አርሶ አደሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀት እንዲችል ያልተቋረጠ የባለሙያዎች እገዛ እየተደረገ መሆኑን ሃላፊው አንስተዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026