
ነቀምቴ፤ መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ):- በምስራቅ ወለጋ ዞን በየ2017/18 የምርት ዘመን የሚውል ከ230 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በምስራቅ ወለጋ ዞን ግብርና ፅህፈት ቤት የግብርና መካናይዜሽን የግብዓት ፍላጎት እና አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ለሚ አጋ እንዳሉት በየ2017/18 ምርት ዘመኑ 800 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ ነው።
በእስካሁኑ ሂደት 65 ሺህ 378 ኩንታል 'ዳፕ' እና 165 ሺህ ኩንታል 'ዩሪያ' የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል።
እንዲሁም 20 ሺህ ኩንታል ምርጥ ዘር ለማቅረብ የታቅዶ ሲሆን እስካሁን 10 ሺህ 50 ኩንታል ለአርሶ አደሩ መድረሱን ጠቅሰው ያለውን ፍላጎት ለሟሟላት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የስርጭቱ ሂደት ከመልካም አስተዳደር ችግር በጸዳ መልኩ እንዲከናወን ሽያጩ በዲጂታል መንገድ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አስፋው ሀንቢሳ፤ በዞኑ በተለያዩ ኢኒሼቲቮች አመቱን ሙሉ የግብርና ስራ እንዲከናወን ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።
በዚህም የዞኑ አርሶ አደር በምግብ ራሱን ከመቻል ባሻገር ለሀገር ውስጥና እና ለውጪ ገበያ የሚውሉ ምርቶችን ማምረት መጀመሩን ጠቁመዋል።
በዞኑ የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ እንዲቀርብ ከማድረግ ባሻገር አርሶ አደሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀት እንዲችል ያልተቋረጠ የባለሙያዎች እገዛ እየተደረገ መሆኑን ሃላፊው አንስተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026