የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በምስራቅ ወለጋ ዞን ከ230 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ቀርቧል

Apr 8, 2025

IDOPRESS

ነቀምቴ፤ መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ):- በምስራቅ ወለጋ ዞን በየ2017/18 የምርት ዘመን የሚውል ከ230 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።

በምስራቅ ወለጋ ዞን ግብርና ፅህፈት ቤት የግብርና መካናይዜሽን የግብዓት ፍላጎት እና አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ለሚ አጋ እንዳሉት በየ2017/18 ምርት ዘመኑ 800 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ ነው።

በእስካሁኑ ሂደት 65 ሺህ 378 ኩንታል 'ዳፕ' እና 165 ሺህ ኩንታል 'ዩሪያ' የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል።

እንዲሁም 20 ሺህ ኩንታል ምርጥ ዘር ለማቅረብ የታቅዶ ሲሆን እስካሁን 10 ሺህ 50 ኩንታል ለአርሶ አደሩ መድረሱን ጠቅሰው ያለውን ፍላጎት ለሟሟላት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የስርጭቱ ሂደት ከመልካም አስተዳደር ችግር በጸዳ መልኩ እንዲከናወን ሽያጩ በዲጂታል መንገድ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።


የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አስፋው ሀንቢሳ፤ በዞኑ በተለያዩ ኢኒሼቲቮች አመቱን ሙሉ የግብርና ስራ እንዲከናወን ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።

በዚህም የዞኑ አርሶ አደር በምግብ ራሱን ከመቻል ባሻገር ለሀገር ውስጥና እና ለውጪ ገበያ የሚውሉ ምርቶችን ማምረት መጀመሩን ጠቁመዋል።

በዞኑ የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ እንዲቀርብ ከማድረግ ባሻገር አርሶ አደሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀት እንዲችል ያልተቋረጠ የባለሙያዎች እገዛ እየተደረገ መሆኑን ሃላፊው አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026