ነቀምቴ፤ መጋቢት 30/2017 (ኢዜአ):- በምስራቅ ወለጋ ዞን በየ2017/18 የምርት ዘመን የሚውል ከ230 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽህፈት ቤት አስታወቀ።
በምስራቅ ወለጋ ዞን ግብርና ፅህፈት ቤት የግብርና መካናይዜሽን የግብዓት ፍላጎት እና አጠቃቀም ቡድን መሪ አቶ ለሚ አጋ እንዳሉት በየ2017/18 ምርት ዘመኑ 800 ሺህ ኩንታል የአፈር ማዳበሪያ ለማቅረብ ታቅዶ እየተሰራ ነው።
በእስካሁኑ ሂደት 65 ሺህ 378 ኩንታል 'ዳፕ' እና 165 ሺህ ኩንታል 'ዩሪያ' የአፈር ማዳበሪያ ለአርሶ አደሩ ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል።
እንዲሁም 20 ሺህ ኩንታል ምርጥ ዘር ለማቅረብ የታቅዶ ሲሆን እስካሁን 10 ሺህ 50 ኩንታል ለአርሶ አደሩ መድረሱን ጠቅሰው ያለውን ፍላጎት ለሟሟላት እየተሰራ ነው ብለዋል።
የስርጭቱ ሂደት ከመልካም አስተዳደር ችግር በጸዳ መልኩ እንዲከናወን ሽያጩ በዲጂታል መንገድ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
የዞኑ ግብርና ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ አስፋው ሀንቢሳ፤ በዞኑ በተለያዩ ኢኒሼቲቮች አመቱን ሙሉ የግብርና ስራ እንዲከናወን ምቹ ሁኔታ መፈጠሩን ተናግረዋል።
በዚህም የዞኑ አርሶ አደር በምግብ ራሱን ከመቻል ባሻገር ለሀገር ውስጥና እና ለውጪ ገበያ የሚውሉ ምርቶችን ማምረት መጀመሩን ጠቁመዋል።
በዞኑ የአፈር ማዳበሪያ በወቅቱ እንዲቀርብ ከማድረግ ባሻገር አርሶ አደሩ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ማዘጋጀት እንዲችል ያልተቋረጠ የባለሙያዎች እገዛ እየተደረገ መሆኑን ሃላፊው አንስተዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025