የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በአማራ ክልል ከ50 ሺህ 600 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ በመስኖ የለማ ስንዴ ተሰበሰበ

Apr 9, 2025

IDOPRESS

ደሴ ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል በዘንደሮ የበጋ ወቅት ከ50 ሺህ 600 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ በመስኖ የለማ የስንዴ ሰብል መሰብሰቡን የክልሉ ግብርና ቢሮ አስታወቀ።

የቢሮው ምክትል ኃላፊ አቶ ቃልኪዳን ሽፈራው ለኢዜአ እንደገለጹት፤በክልሉ ያሉትን የውሃ አማራጮች በመጠቀም በዘንድሮው የበጋ ወቅት ከ202 ሺህ ሄክታር መሬት በላይ በበጋ መስኖ ስንዴ ለምቷል፡፡

እስከ አሁንም ከ50 ሺህ 600 ሄክታር በሚበልጥ መሬት ላይ ለምቶ የደረሰ ሰብል መሰብሰብ መቻሉን አስታውቀዋል።

አርሶ አደሩም የደረሰውን ቀሪ ሰብል እየጣለ ካለው ዝናብ ለመከላከል በፍጥነት መሰብሰብ እንዳለበት አሳስበዋል።


በደቡብ ወሎ ዞን አርጎባ ብሄረሰብ ልዩ ወረዳ የ07 ቀበሌ አርሶ አደር ሰይድ አሊ በሰጡት አስተያየት፤ በአንድ ሄክታር ከሩብ ማሳቸው ላይ በመስኖ ያለሙትን ስንዴ መሰብሰባቸውን ገልጸዋል፡፡

በበጋ መስኖ አንድ ሄክታር የሚጠጋ መሬት ላይ ያለሙት ስንዴን እየሰበሰቡ እንደሚገኙ የተናገሩት ደግሞ በቃሉ ወረዳ 032 ቀበሌ አርሶ አደር ይማም አደም ናቸው፡፡

የደረሰውን ሰብል በጥንቃቄ በመሰብሰብ ከ20 ኩንታል በላይ ምርት እንደሚጠብቁም ጠቁመዋል፡፡

በአማራ ክልል ባለፈው ዓመት በበጋ መስኖ በስንዴ ሰብል ከለማው 159 ሺህ ሄክታር መሬት ከአምስት ነጥብ አራት ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

በ2017/2018 ምርት ዘመን የመኸር ሰብል ልማት እቅድን ለማሳካት በግብርና ፓኬጅ አተገባበር ላይ ያተኮረ ስልጠናና የእቅድ ትውውቅ ማጠቃለያ መድረክ ሰሞኑን በደሴ ከተማ መካሄዱ ይታወሳል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026