የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አገልግሎት አስጀመረ

Apr 9, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 30/2017(ኢዜአ):- ኢትዮ ቴሌኮም ሁለተኛውንና እጅግ ፈጣን የሆነውን የኤሌክትሪክ መኪና ባትሪ መሙያ ጣቢያ አገልግሎት ዛሬ በአዲስ አበባ ማስጀመሩን አስታወቀ።

ለሀገር እድገት ቁልፍ የሆኑ ዘርፎችን የማዘመን ጥረቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጿል።

ከመገናኛ - ቦሌ አንበሳ ጋራጅ ፊት ስራ የጀመረው ጣቢያ የአውሮፓ ስሪት የሆኑ መኪኖችን የኤሌክትሪክ ኃይል መሙላት የሚያስችል እጅግ ፈጣን (EU Altra Fast) አቅም ያለው መሆኑም ተጠቁሟል።

የኤሌክትሪክ መኪና መሙያዎቹ በ1 ሰከንድ 1 ኪሎ ሜትር መጓዝ የሚያስችል የኤሌክትሪክ ኃይል በመሙላት በ15 ደቂቃ ውስጥ ሙሉ (100%) የኤሌክትሪክ ኃይል የመሙላት አቅም እንዳላቸው ተመላክቷል።

እንዲሁም በሰው ሰራሽ አስተውሎት(AI) ቴክኖሎጂ የባትሪ መስፈርቶች እና የደንበኛን ትዕዛዝ በመተንተን የባትሪውን ደህንነት እየፈተሸ የተሽከርካሪው ባትሪ በሚችለው ፍጥነት ቻርጅ እንደሚያደርግም ነው ድርጅቱ ያስታወቀው።

የኤሌክትሪክ ጣቢያው ለ24 ሰዓት አገልግሎት እንደሚሰጥና አገልግሎቱን በቴሌብር ሱፐርአፕ አማካኝነት መጠቀምና የአገልግሎት ክፍያ መፈጸም የሚያስችል እንደሆነም ተጠቁሟል።

ኩባንያው ቀደም ሲል 16 መኪኖችን ማስተናገድ የሚችል ጣቢያ ወደ ስራ ማስገባቱን አስታውሶ ከየካቲት 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ14 ሺህ 280 የኤሌክትሪክ መኪኖች በኪሎ ዋት 376 ሺህ 575 ኃይል ቻርጅ ማድረግ መቻሉን ገልጿል።

ይህም የአየር ብክለትን ከመከላከል አንጻር ከ521 ሺህ በላይ ኪሎ ግራም ካርቦንዳይ ኦክሳይድ ወደ ከባቢ አየር እንዳይለቀቅ ማድረግ መቻሉንና ይህም ከ2 ሺህ 622 በላይ ዛፎችን ከመትከል ጋር የሚስተካከል እንደሆነ አመልክቷል።

አዲሱ የመሙያ ጣቢያ 16 መሙያዎችን ማካቱንና ይህም ኩባንያው ያሉትን የኤሌክትሪክ መኪና መሙያ ጣቢያዎች የማስተናገድ አቅም ወደ 32 ማድረስ መቻሉን አብራርቷል።

ኢትዮ ቴሌኮም ለዘላቂ እድገት ወሳኝ የሆኑ ቀጣይነት ያላቸው የዲጂታል መሠረተ ልማቶችን እና ፈጠራዎችን በማስተዋወቅ ለሀገር እድገት ቁልፍ የሆኑ ዘርፎችን የማዘመን ጥረቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025