
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ የውሃ ቆጣሪ ፍላጎትን በሀገር ውስጥ ምርት በማሟላት ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ፡፡
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል የውኃ ቆጣሪ ምርት ላይ የተሰማራውን ሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግን ጎብኝተዋል፡፡

በዚሁ ወቅት አቶ መላኩ አለበል እንደተናገሩት፤ መንግስት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካትና ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶች በስፋት እንዲመረቱ እየሰራ ይገኛል፡፡
በዚህም በኢንጂነሪንግ ዘርፍ እና በሌሎች ተኪ ምርቶችን የሚያመርቱ ፋብሪካዎችን የማስፋፋት እና የማጠናከር ስራ መሰራቱን ገልጸዋል፡፡
ዛሬ የጎበኙት የውኃ ቆጣሪ ማምረቻ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በማስቀረት በኩል ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡
በዚህም በሚቀጥሉት አመታት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን በማሟላት ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የሚያመርቱ ፋብሪካዎች እንዲስፋፉ ከማድረግ አንጻር ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ እንዳሉት ከተሞችም ጭምር የተለያዩ የፋብሪካ ምርቶች የሚመረትባቸው መሆን እዳለባቸው ተናግረዋል።

የሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ስራ አስኪያጅ ዐይንእሸት አስረስ(ዶ/ር) በበኩላቸው ድርጅቱ በቀን ከ800 እስከ 1000 የውሃ ቆጣሪ እያመረተ ለሀገር ውስጥ ገበያ እያቀረበ ይገኛል ብለዋል።
በቀጣይም የምርቱን መጠን በማሳደግ ወደ ጎረቤት ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የኢትየጵያ ታምርት ንቅናቄ ለውጤታማነታቸው ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን አንስተው የመንግስት ድጋፍም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026