
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ የውሃ ቆጣሪ ፍላጎትን በሀገር ውስጥ ምርት በማሟላት ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ፡፡
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል የውኃ ቆጣሪ ምርት ላይ የተሰማራውን ሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግን ጎብኝተዋል፡፡

በዚሁ ወቅት አቶ መላኩ አለበል እንደተናገሩት፤ መንግስት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካትና ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶች በስፋት እንዲመረቱ እየሰራ ይገኛል፡፡
በዚህም በኢንጂነሪንግ ዘርፍ እና በሌሎች ተኪ ምርቶችን የሚያመርቱ ፋብሪካዎችን የማስፋፋት እና የማጠናከር ስራ መሰራቱን ገልጸዋል፡፡
ዛሬ የጎበኙት የውኃ ቆጣሪ ማምረቻ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በማስቀረት በኩል ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡
በዚህም በሚቀጥሉት አመታት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን በማሟላት ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የሚያመርቱ ፋብሪካዎች እንዲስፋፉ ከማድረግ አንጻር ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ እንዳሉት ከተሞችም ጭምር የተለያዩ የፋብሪካ ምርቶች የሚመረትባቸው መሆን እዳለባቸው ተናግረዋል።

የሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ስራ አስኪያጅ ዐይንእሸት አስረስ(ዶ/ር) በበኩላቸው ድርጅቱ በቀን ከ800 እስከ 1000 የውሃ ቆጣሪ እያመረተ ለሀገር ውስጥ ገበያ እያቀረበ ይገኛል ብለዋል።
በቀጣይም የምርቱን መጠን በማሳደግ ወደ ጎረቤት ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የኢትየጵያ ታምርት ንቅናቄ ለውጤታማነታቸው ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን አንስተው የመንግስት ድጋፍም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026