
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ የውሃ ቆጣሪ ፍላጎትን በሀገር ውስጥ ምርት በማሟላት ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ፡፡
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል የውኃ ቆጣሪ ምርት ላይ የተሰማራውን ሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግን ጎብኝተዋል፡፡

በዚሁ ወቅት አቶ መላኩ አለበል እንደተናገሩት፤ መንግስት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካትና ለውጪ ገበያ የሚቀርቡ ምርቶች በስፋት እንዲመረቱ እየሰራ ይገኛል፡፡
በዚህም በኢንጂነሪንግ ዘርፍ እና በሌሎች ተኪ ምርቶችን የሚያመርቱ ፋብሪካዎችን የማስፋፋት እና የማጠናከር ስራ መሰራቱን ገልጸዋል፡፡
ዛሬ የጎበኙት የውኃ ቆጣሪ ማምረቻ ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በማስቀረት በኩል ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል፡፡
በዚህም በሚቀጥሉት አመታት የሀገር ውስጥ ፍላጎትን በማሟላት ለውጭ ገበያ ለማቅረብ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ተኪ ምርት የሚያመርቱ ፋብሪካዎች እንዲስፋፉ ከማድረግ አንጻር ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝም ገልጸዋል፡፡
ሚኒስትሩ እንዳሉት ከተሞችም ጭምር የተለያዩ የፋብሪካ ምርቶች የሚመረትባቸው መሆን እዳለባቸው ተናግረዋል።

የሳቢያን ቤዝ ሜታል ኢንጂነሪንግ ኃ.የተ.የግ.ማህበር ስራ አስኪያጅ ዐይንእሸት አስረስ(ዶ/ር) በበኩላቸው ድርጅቱ በቀን ከ800 እስከ 1000 የውሃ ቆጣሪ እያመረተ ለሀገር ውስጥ ገበያ እያቀረበ ይገኛል ብለዋል።
በቀጣይም የምርቱን መጠን በማሳደግ ወደ ጎረቤት ሀገራት በመላክ የውጭ ምንዛሬ ለማግኘት ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የኢትየጵያ ታምርት ንቅናቄ ለውጤታማነታቸው ትልቅ አስተዋጽኦ ማድረጉን አንስተው የመንግስት ድጋፍም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026