
አሶሳ፤ሚያዝያ 1/2017(ኢዜአ):-በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን ተናገሩ።
ዘጠነኛው ክልል አቀፍ የግብርና ዘርፍ ባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ በአሶሳ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰን የአርሶ አደሩን የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀም በማሻሻል ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።
አርሶአደሩ ከማሳ ዝግጅት ጀምሮ የግብዓት አጠቃቀም ባህሉን በመቀየር በምርት ዘመኑ አበረታች የግብርና እንቅስቃሴ ሲያደርግ እንደነበር ጠቅሰዋል።
ህብረተሰቡን ከተረጂነት ለመላቀቅና በቤተሰብ ደረጃ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የተቀረፁ የልማት ኢንሼቲቮችም ተስፋ ሰጪ ውጤት እያሳዩ መሆናቸውን ጠቁመው፤በተለይም በሌማት ትሩፋት እና በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር የተገኙ ውጤቶች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
ለአብነትም የፈሳሽ ናይትሮጂን ምርት መጀመርና የእንስሳት መኖ አቅርቦት ማሻሻልም የግብርናውን ዘርፍ ለማዘመን የተከናወኑ ተግባራት መሆናቸውን አብራርተዋል።
የክልሉ የግብርና ትራንስፎርሜሽን ፍኖተ ካርታ የግብርናውን ዘርፍ ከዚህ በተሻለ እንደሚያሳድገውም አቶ አሻድሊ ጠቁመዋል።
አርሶ አደሩ የኩታ ገጠም እርሻን እንዲላመድ መደረጉ ትልቅ ለውጥ መሆኑን የተናገሩት አቶ አሻድሊ፥ ክልሉ ካለው ምቹ የእርሻ ማሳ አንፃር የኩታ ገጠም እርሻን አሁንም ማሳደግ ይገባል ነው ያሉት።
በ2017/18 የምርት ዘመን 1 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር ማሳ በዘር ለመሸፈን ዕቅድ መያዙን አቶ አሻድሊ ገልጸዋል።
የግብርናው ዘርፍ ባለድርሻ አካላትም የዘርፉን ችግሮች በመለየት እና የምርምር ስራዎችን በማጠናከር ምርታማነትን ለማሳደግ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ ጠይቀዋል።
በመድረኩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣የግብርናው ዘርፍ ባለድርሻ አካላት እና የምርምር ተቋማት ተወካዮች ተገኝተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026