የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር መስመር ደህንነት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በአፋር ክልል አዋሽ ሰባት በኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር መስመር ደህንነት ዙሪያ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ውይይት እድርገዋል።

ሚኒስትሩ በተለይ በቅርብ ጊዜ በባቡሩ ኤሌክትሪክ መስመር ላይ ጉዳት እና ስርቆት መድረሱን ተከትሎ ችግሩን ለመፍታት ከአካባቢው ሃይማኖት አባቶች፣ ከጎሳ መሪዎች፣ ከፀጥታ አካላት እና ከተለያዩ ስራ ኃላፊዎች ጋር መክረዋል።

የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር መስመር ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመፍታትና ባቡሩን በሙሉ አቅም መጠቀም እንዲቻል የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ስራ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።


የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በበኩላቸው ችግሩ እንዲፈጠር ያደረጉ አካላትን በትብብር የማጥራት ስራ መከናወን እዳለበት ገልጸዋል።

በባቡር መስመሩ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ከፌዴራል መንግስት፣ ከክልል መንግስታት፣ ከፀጥታ አካላት፣ ከኢትዮጵያ መብራት ሀይል እና ከሌሎች አካላት ጋር በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በባቡር መስመሩ ላይ ጉዳት በማድረስ ስርቆት በሚፈፅሙ አካላት ላይ ከመንግሥት ጎን በመሆን የማጋለጥ ስራ እያከናወኑ መሆኑን መግለጻቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025