የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር መስመር ደህንነት ዙሪያ ውይይት ተካሄደ

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ(ዶ/ር) በአፋር ክልል አዋሽ ሰባት በኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር መስመር ደህንነት ዙሪያ ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር ውይይት እድርገዋል።

ሚኒስትሩ በተለይ በቅርብ ጊዜ በባቡሩ ኤሌክትሪክ መስመር ላይ ጉዳት እና ስርቆት መድረሱን ተከትሎ ችግሩን ለመፍታት ከአካባቢው ሃይማኖት አባቶች፣ ከጎሳ መሪዎች፣ ከፀጥታ አካላት እና ከተለያዩ ስራ ኃላፊዎች ጋር መክረዋል።

የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር መስመር ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን በመፍታትና ባቡሩን በሙሉ አቅም መጠቀም እንዲቻል የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ ስራ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።


የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር ትራንስፖርት አክሲዮን ማህበር ዋና ስራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ታከለ ኡማ በበኩላቸው ችግሩ እንዲፈጠር ያደረጉ አካላትን በትብብር የማጥራት ስራ መከናወን እዳለበት ገልጸዋል።

በባቡር መስመሩ ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመፍታት ከፌዴራል መንግስት፣ ከክልል መንግስታት፣ ከፀጥታ አካላት፣ ከኢትዮጵያ መብራት ሀይል እና ከሌሎች አካላት ጋር በቅንጅት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በባቡር መስመሩ ላይ ጉዳት በማድረስ ስርቆት በሚፈፅሙ አካላት ላይ ከመንግሥት ጎን በመሆን የማጋለጥ ስራ እያከናወኑ መሆኑን መግለጻቸውን የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026