የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግብርናውን ዘርፍ የበለጠ ውጤታማ ለማድረግ በቅንጅት ይሰራል

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አሶሳ፤ ሚያዝያ 1/2017(ኢዜአ):- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ይበልጥ ለማሳደግ በቅንጅት ይሰራል ሲሉ የዘርፉ አመራሮች ተናገሩ።

ዘጠነኛው ክልል አቀፍ የግብርና ዘርፍ ባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ በአሶሳ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ የዘርፉ ጠንካራ እና ደካማ ጎን የተገመገመ ሲሆን ለ2017/18 የምርት ዘመን አርሶ አደሩ የግብርና ስራውን በተሻለ መልኩ መተግበር እንዳለበት አቅጣጫ ተቀምጧል።

ኢዜአ ያነጋገራቸው የመድረኩ ተሳታፊዎች በክልሉ የግብርና ዘርፉን ውጤታማ ለማድረግ ቅንጅታዊ አሰራርን ማጠናከር ይገባል ብለዋል።


ከተሳታፊዎቹ መካከል የመተከል ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ ሙሉጌታ አባይ በክልሉ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚደረጉ ጥረቶች ውጤታማ መሆናቸውን ተናግረዋል።

መድረኩም የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የግብርና ዘርፉ እንዲዘምን እና የአርሶ አደሩ ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እንዲረጋገጥ ግብዓት የተወሰደበት ነው ብለዋል።

የአሶሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ዳይሬክተር አቶ ደስታ በቀለ በበኩላቸው በክልሉ የግብርናውን ዘርፍ ውጤታማ ለማድረግ ማዕከሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ እና በማላመድ የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል።


ማዕከሉ በቅርቡ ያወጣቸውን የበርበሬ እና ከርከዴ ምርቶች ወደ አርሶ አደሩ ለማድረስ እየሰራ መሆኑን የተናገሩት ዳይሬክተሩ፤ በሰሊጥ እና በማሽላ ምርቶች ላይም በስፋት ለመስራት ዕቅድ መያዙን ጠቁመዋል።

ለስራው ስኬታማነት ከግብርና ቢሮ ጋር በቅንጅት እየሰሩ መሆናቸውን በመጠቆም።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል 3 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሄክታር ማሳ ለእርሻ ተስማሚ ቢሆንም እስካሁን ማልማት የተቻለው 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን ሄክታር ማሳ ብቻ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በክልሉ ግብርና ቢሮ የግብርና ኤክስቴንሽን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አብዱሰላም አብዱልጀሊል ናቸው።


አርሶ አደሩ የሜካናይዜሽን ቴክኖሎጂ በመጠቀም የግብርና ስራውን በስፋት እንዲያከናውን ለማድረግ ከሌሎች ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል።

በአሁኑ ሰዓት በክልሉ የምርጥ ዘር እና የአፈር ማዳበሪያ አቅርቦት መኖሩን ጠቅሰው አርሶ አደሩ በወቅቱ እንዲጠቀም እና የእርሻ ማሳውን እንዲያዘጋጅ አሳስበዋል።

ዘጠነኛው ክልል አቀፍ የግብርና ዘርፍ የባለድርሻ አካላት መድረክ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የግብርናው ዘርፍ ባለድርሻ አካላት እና የምርምር ተቋማት ተወካዮች በተገኙበት ተካሂዷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026