የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የናይጄሪያ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በኢንቨስትመንት ዘርፍ የመሰማራት ፍላጎትን ጨምሯል

Apr 10, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የናይጄሪያ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች የመሰማራት ፍላጎት ማሳደጉን በኢትዮጵያ የናይጄሪያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን ኃላፊ አምባሳዶር ማክስ ኦቤዴ ገለጹ።

ምክትል ሚሲዮን ኃላፊው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያና ናይጄሪያ የረጅም ጊዜ ስትራቴጂክ አጋርነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን አንስተዋል።

የሁለቱ ሀገራት የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ትስስሩን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩም ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ ያደረገችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የናይጄሪያ ባለሃብቶችን ቀልብ መሳቡን ተናግረዋል።

ማሻሻያውን ተከትሎ በርካታ የናይጄሪያ ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በዘርፉ የመሰማራት ፍላጎት መጨመሩንም ገልጸዋል።

የሁለቱ ሀገራት የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት ቀደም ሲል የጀመረ መሆኑን ጠቁመው፤ የናይጄሪያ ባለሃብቶች በሲሚንቶ ምርት፣ በምግብና መጠጥ ዘርፎች መሰማራታቸውን አንስተዋል።

የተደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ የባንክ ዘርፉን ጨምሮ በርካታ የናይጄሪያ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ነው የተናገሩት።

እንደ ምክትል አምባሳደሩ ገለጻ ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ በርካታ የህዝብ ቁጥርና ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው ናቸው።

ሀገራቱ በቀጣይም በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ግንኙነታቸውን የበለጠ በማጠናከር በአፍሪካ የመሪነት ሚናቸውን ይወጣሉ ብለዋል።

ሀገራቱ የብዝሃ ባህል፣ ሃይማኖት እና ቋንቋ ባለቤት መሆናቸውን ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድም በሳምንት ሶሰት ቀን ወደ ናይጄሪያ የሚያደርገው በረራ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን የበለጠ ለማጠናከር ወሳኝ ሚና አለው ነው ያሉት።

ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ የጀመሩት እአአ በ1964 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026