
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 1/2017(ኢዜአ)፦ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የናይጄሪያ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች የመሰማራት ፍላጎት ማሳደጉን በኢትዮጵያ የናይጄሪያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን ኃላፊ አምባሳዶር ማክስ ኦቤዴ ገለጹ።
ምክትል ሚሲዮን ኃላፊው ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ኢትዮጵያና ናይጄሪያ የረጅም ጊዜ ስትራቴጂክ አጋርነት ያላቸው ሀገራት መሆናቸውን አንስተዋል።
የሁለቱ ሀገራት የንግድና ኢንቨስትመንት ትስስር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተሻሻለ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ትስስሩን ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰሩም ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ያደረገችው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ የናይጄሪያ ባለሃብቶችን ቀልብ መሳቡን ተናግረዋል።
ማሻሻያውን ተከትሎ በርካታ የናይጄሪያ ባለሃብቶች ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በዘርፉ የመሰማራት ፍላጎት መጨመሩንም ገልጸዋል።
የሁለቱ ሀገራት የንግድና ኢንቨስትመንት ግንኙነት ቀደም ሲል የጀመረ መሆኑን ጠቁመው፤ የናይጄሪያ ባለሃብቶች በሲሚንቶ ምርት፣ በምግብና መጠጥ ዘርፎች መሰማራታቸውን አንስተዋል።
የተደረገውን የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ተከትሎ የባንክ ዘርፉን ጨምሮ በርካታ የናይጄሪያ ባለሃብቶች በኢትዮጵያ የመስራት ፍላጎት እንዳላቸው ነው የተናገሩት።
እንደ ምክትል አምባሳደሩ ገለጻ ሁለቱ ሀገራት በአፍሪካ በርካታ የህዝብ ቁጥርና ግዙፍ ኢኮኖሚ ያላቸው ናቸው።
ሀገራቱ በቀጣይም በጋራ ጥቅም ላይ የተመሰረተ ግንኙነታቸውን የበለጠ በማጠናከር በአፍሪካ የመሪነት ሚናቸውን ይወጣሉ ብለዋል።
ሀገራቱ የብዝሃ ባህል፣ ሃይማኖት እና ቋንቋ ባለቤት መሆናቸውን ጠቅሰው፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድም በሳምንት ሶሰት ቀን ወደ ናይጄሪያ የሚያደርገው በረራ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነቱን የበለጠ ለማጠናከር ወሳኝ ሚና አለው ነው ያሉት።
ኢትዮጵያ እና ናይጄሪያ የዲፕሎማሲ ግንኙነታቸውን በይፋ የጀመሩት እአአ በ1964 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026