
ጋምቤላ፤ሚያዝያ 2/2017(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ከተማ ለተጀመረው የኮሪደር ልማት ስኬታማነት የህዝቡና የባለሀብቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።
የጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።

ርዕሰ መስተዳደሯ በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንዳሉት የከተሞችን ልማት ለማዘመንና ለኑሮ ምቹና ውብ ለማድረግ ለተጀመረው የኮሪደር ልማት መሳካት የህዝቡና የባለሃብቱ ድጋፍና ትብብር ሊጠናከር ይገባል።
የከተሞች ልማት መዘመን ለገጽታ ግንባታና ለኑሮ ምቹ ከመሆን ባለፈ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪውና ለስራ እድል ፈጠራ ጭምር የጎላ ፋይዳ ያለው መሆኑንም ተናግረዋል።

በመሆኑም የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች በመንግስት ብቻ ስኬታማ ስለማይሆኑ የህብረተሰቡና የባለሀብቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ድጋፍ ወሳኝ ነው ብለዋል።
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሰይመን ሙን(ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከጀመራቸው ስራዎች መካከል የኮርደር ልማት አንዱ ነው ብለዋል።

ይህን ታሳቢ በማድረግ ከተማ አስተዳደሩ የጋምቤላ ከተማን ልማት በማዘመን ውብና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል ።
በገቢ በማስጀመሪያ መረሃ ግብሩ ላይ የክልሉ፣ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ባለሃብቶች ተገኝተዋል ።
በጋምቤላ ከተማ በመጀመሪያ ዙር በአራት አቅጣጫ 14 ኪሎ ሜትር የሚሸፋን የኮሪደር ልማት ተጀምሯል ።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026