
ጋምቤላ፤ሚያዝያ 2/2017(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ከተማ ለተጀመረው የኮሪደር ልማት ስኬታማነት የህዝቡና የባለሀብቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።
የጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።

ርዕሰ መስተዳደሯ በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንዳሉት የከተሞችን ልማት ለማዘመንና ለኑሮ ምቹና ውብ ለማድረግ ለተጀመረው የኮሪደር ልማት መሳካት የህዝቡና የባለሃብቱ ድጋፍና ትብብር ሊጠናከር ይገባል።
የከተሞች ልማት መዘመን ለገጽታ ግንባታና ለኑሮ ምቹ ከመሆን ባለፈ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪውና ለስራ እድል ፈጠራ ጭምር የጎላ ፋይዳ ያለው መሆኑንም ተናግረዋል።

በመሆኑም የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች በመንግስት ብቻ ስኬታማ ስለማይሆኑ የህብረተሰቡና የባለሀብቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ድጋፍ ወሳኝ ነው ብለዋል።
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሰይመን ሙን(ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከጀመራቸው ስራዎች መካከል የኮርደር ልማት አንዱ ነው ብለዋል።

ይህን ታሳቢ በማድረግ ከተማ አስተዳደሩ የጋምቤላ ከተማን ልማት በማዘመን ውብና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል ።
በገቢ በማስጀመሪያ መረሃ ግብሩ ላይ የክልሉ፣ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ባለሃብቶች ተገኝተዋል ።
በጋምቤላ ከተማ በመጀመሪያ ዙር በአራት አቅጣጫ 14 ኪሎ ሜትር የሚሸፋን የኮሪደር ልማት ተጀምሯል ።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026