
ጋምቤላ፤ሚያዝያ 2/2017(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ከተማ ለተጀመረው የኮሪደር ልማት ስኬታማነት የህዝቡና የባለሀብቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎ ሊጠናከር እንደሚገባ የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።
የጋምቤላ ከተማ የኮሪደር ልማት የገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ ግብር ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ተካሂዷል።

ርዕሰ መስተዳደሯ በመርሃ ግብሩ ማስጀመሪያ ላይ እንዳሉት የከተሞችን ልማት ለማዘመንና ለኑሮ ምቹና ውብ ለማድረግ ለተጀመረው የኮሪደር ልማት መሳካት የህዝቡና የባለሃብቱ ድጋፍና ትብብር ሊጠናከር ይገባል።
የከተሞች ልማት መዘመን ለገጽታ ግንባታና ለኑሮ ምቹ ከመሆን ባለፈ ለቱሪዝም ኢንዱስትሪውና ለስራ እድል ፈጠራ ጭምር የጎላ ፋይዳ ያለው መሆኑንም ተናግረዋል።

በመሆኑም የተጀመሩ የኮሪደር ልማት ስራዎች በመንግስት ብቻ ስኬታማ ስለማይሆኑ የህብረተሰቡና የባለሀብቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ድጋፍ ወሳኝ ነው ብለዋል።
የጋምቤላ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሰይመን ሙን(ዶ/ር) በበኩላቸው መንግስት የህዝብን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከጀመራቸው ስራዎች መካከል የኮርደር ልማት አንዱ ነው ብለዋል።

ይህን ታሳቢ በማድረግ ከተማ አስተዳደሩ የጋምቤላ ከተማን ልማት በማዘመን ውብና ለኑሮ ምቹ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል ።
በገቢ በማስጀመሪያ መረሃ ግብሩ ላይ የክልሉ፣ የዞንና የወረዳ ከፍተኛ አመራሮችን ጨምሮ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችና ባለሃብቶች ተገኝተዋል ።
በጋምቤላ ከተማ በመጀመሪያ ዙር በአራት አቅጣጫ 14 ኪሎ ሜትር የሚሸፋን የኮሪደር ልማት ተጀምሯል ።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026