የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከአንድ ሚሊዮን በላይ ዜጎች በገበያ መረጃ ስርዓት ተመዝግበዋል -የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር

Apr 11, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ):-ባለፉት ዘጠኝ ወራት 1 ሚሊዮን 422 ሺህ በላይ ዜጎች በገበያ መረጃ ስርዓት መመዝገባቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ።


ስድስተኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አራተኛ ዓመት የስራ ዘመን 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን ያካሄደ ሲሆን፤የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን አዳምጧል ።


የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ከሚል በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ሚኒስቴሩ በ2017 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ልማት፣በኢንዱስትሪ ሰላም እንዲሁም በተቋም ግንባታ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ተግባራት አከናውኗል።


ተቋማዊ የሪፎርም ተግባራትን እንደምቹ ሁኔታ በመውሰድ እቅድ በማዘጋጀት በየዘርፉ ያለውን መዋቅር በመጠቀም ሰፋ ያለ የባለድርሻ ተሳትፎን በማረጋገጥ ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል።


ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራት የዘርፉን ተልዕኮ ለመፈፀም የተሻለ መደላድል መፍጠር መቻሉንም ጠቁመዋል።


በሚኒስቴሩ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የተቋማዊ ሪፎርም ሥራዎችን በማፅናት ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል የስልጠናና ምክክር መድረክ መካሄዱን ተናግረዋል።


ባለፉት ዘጠኝ ወራት 1 ሚሊዮን 422 ሺህ በላይ ዜጎች በገበያ መረጃ ስርዓት መመዝገባቸውን ገልፀው፤ ስርዓቱ በአገር ውስጥ የሥራ እድል ለመፍጠር፣ለውጭ አገር የስራ ስምሪት እና ሌሎች አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል።


በዚሁ ስርዓት 110 የፖሊ ቴክኒክ ተቋማት የተማሪዎች ቅበላ ለማከናወን የሚያስችል ስራ መጀመሩንም ተናግረዋል።


ለአገር ውስጥና ውጭ አገር ስራ ስምሪት 3 ሚሊየን 300 ሺህ በላይ ዜጎችን የአጫጭር ስልጠና መስጠት ታቅዶ 3 ሚሊየን 170 ሺህ በላይ ዜጎችን ማሰልጠን መቻሉንም ገልፀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026