አዲስ አበባ፤ሚያዚያ 2/2017 (ኢዜአ):-ባለፉት ዘጠኝ ወራት 1 ሚሊዮን 422 ሺህ በላይ ዜጎች በገበያ መረጃ ስርዓት መመዝገባቸውን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ።
ስድስተኛው የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አራተኛ ዓመት የስራ ዘመን 23ኛ መደበኛ ስብሰባውን ያካሄደ ሲሆን፤የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርቱን አዳምጧል ።
የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ሙፈሪያት ከሚል በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ሚኒስቴሩ በ2017 በጀት ዓመት ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሥራ ዕድል ፈጠራና ክህሎት ልማት፣በኢንዱስትሪ ሰላም እንዲሁም በተቋም ግንባታ ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ተግባራት አከናውኗል።
ተቋማዊ የሪፎርም ተግባራትን እንደምቹ ሁኔታ በመውሰድ እቅድ በማዘጋጀት በየዘርፉ ያለውን መዋቅር በመጠቀም ሰፋ ያለ የባለድርሻ ተሳትፎን በማረጋገጥ ወደ ተግባር መገባቱን ገልጸዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ተግባራት የዘርፉን ተልዕኮ ለመፈፀም የተሻለ መደላድል መፍጠር መቻሉንም ጠቁመዋል።
በሚኒስቴሩ የተጀመሩ የሪፎርም ስራዎችን ውጤታማ ለማድረግ የተቋማዊ ሪፎርም ሥራዎችን በማፅናት ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል የስልጠናና ምክክር መድረክ መካሄዱን ተናግረዋል።
ባለፉት ዘጠኝ ወራት 1 ሚሊዮን 422 ሺህ በላይ ዜጎች በገበያ መረጃ ስርዓት መመዝገባቸውን ገልፀው፤ ስርዓቱ በአገር ውስጥ የሥራ እድል ለመፍጠር፣ለውጭ አገር የስራ ስምሪት እና ሌሎች አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚያስችል መሆኑን አመልክተዋል።
በዚሁ ስርዓት 110 የፖሊ ቴክኒክ ተቋማት የተማሪዎች ቅበላ ለማከናወን የሚያስችል ስራ መጀመሩንም ተናግረዋል።
ለአገር ውስጥና ውጭ አገር ስራ ስምሪት 3 ሚሊየን 300 ሺህ በላይ ዜጎችን የአጫጭር ስልጠና መስጠት ታቅዶ 3 ሚሊየን 170 ሺህ በላይ ዜጎችን ማሰልጠን መቻሉንም ገልፀዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025