የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በምዕራብ ሸዋ ዞን የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በስፋት እየተከናወነ ነው

Apr 11, 2025

IDOPRESS

አምቦ፤ሚያዚያ 2/2017( ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት በስፋት እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ አስተዳደር ገለጸ።


በዞኑ ቶኬ ኩታዬ ወረዳ አመራሮችና ህብረተሰቡ የተሳተፉበት በስድስት ሄክታር መሬት ላይ የሙዝ ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ተከናውኗል።


በችግኝ ተካላ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የምዕራብ ሸዋ ዞን ምክትል አስተዳደሪ አቶ አበበ ጨመዳ እንደገለጹት፥ በዞኑ የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት እምብዛም የተለመደ አይደለም።


ባለፉት ጥቂት ዓመታት ግን የክልሉ መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ከጥራጥሬ ሰብሎች ባሻገር በአትልትና ፍራፍሬ ልማት የተሻለ እንቅስቃሴ ሲደረግ መቆየቱን ገልጸዋል።


የአትክልትና ፍራፍሬ ልማቱ በክረምት ዝናብ ብቻ ሳይሆን በበጋ መስኖም በስፋት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸው፥ በዚህ ዓመትም በበጋ መስኖ 145 ሺህ የሙዝ ችግኝ መተከሉን አረጋግጠዋል።


የዞኑ ኢርሻና ተፈጥሮ ሀብት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተረፈ አራርሳ በበኩላቸው በዞኑ በሚገኙ ዘጠኝ ወረዳዎች የሙዝ ችግኝን ጨምሮ ሌሎች የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኝ ተከላ ሲካሄድ መቆየቱን ጠቅሰዋል።


ከዚህ በፊት የዞኑ አርሶ አደሮች በዓመት አንዴ ብቻ የጥራጥሬ ሰብሎችን ያመርቱ እንደነበር ያነሱት ሀላፊው ባለፉት ሶስት ዓመታት 19 ሚሊየን የአትልትና ፍራፍሬ ችግኝ መተከሉን ገልጸዋል።


ዘንድሮም 22 ሚሊየን የአትክልትና ፍራፍሬ ችግኝ ለመትከል ህብረተሰቡን ባሳተፈ መልኩ ስራው ተጠናክሮ መጠቀሉን አስረድተዋል።


ከአርሶ አደሮች ባለፈ ወጣቶችን በማህበር በማደራጀት በልማቱ እንዲሳተፉ እየተደረገ መሆኑን አክለዋል።


የወረዳው አርሶ አደሮች የሙዝ ልማት ውስጥ እንዲሳተፉ በተደረገው ጥረት አሁን ላይ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴዎች መታየታቸውን የተናገሩት ደግሞ የቶኬ ኩታዬ ወረዳ እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ጽህፈት ቤት የቡና እና ሆርቲካልቸር ልማት ቡድን መሪ አቶ አብዲሳ ሂርጳሳ ናቸው።


በአሁኑ ወቅትም የወረዳው አርሶ አደሮች ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በትልትና ፍራፍሬ ልማት በስፋት እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል።


በአትልትትና ፍራፍሬ ማልማት የጀመሩ አርሶ አደሮችም ልማቱ የተሻለ ተጠቃሚ እንደሚያደርጋቸው ተስፋ በማድርግ በስራው እየተሳተፉ መሆኑን ተናግረዋል።


በዚህ ወቅት በክላስተር ተደራጅተው ሙዝን ጨምሮ የተለያዩ አትክልትና ፍራፍሬዎችን ማልማት መጀመራቸውን ገልጸው የወረዳው እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ጽህፈት ቤትም አስፈላጊ ድጋፍ እያደረገላቸው መሆኑን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026