አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በሀገር አቀፍ ደረጃ 215 ሺህ ቶን ማር መመረቱን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የሌማት ትሩፋት መርኃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ ከማር ምርት ከፍተኛ ውጤት መገኘቱን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ(ዶ/ር) ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 210 ሺህ ቶን ማር ለማምረት እቅድ መያዙን አስታውሰው በአፈጻጸም ረገድ 215 ሺህ ቶን ማር በማምረት ከእቅድ በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል።
በሌማት ትሩፋት መርኃ ግብር ጥሩ ውጤት ከተገኘባቸው ምርቶች አንዱ ማር መሆኑንም አስታውቀዋል።
አፈጻጸሙን የበለጠ ለማሳደግ ባህላዊ ቀፎችን ወደ ዘመናዊ ቀፎ የመለወጥ ሥራ በስፋት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
ከአንድ ባህላዊ ቀፎ የሚገኘው ምርት ከ10 ኪሎ ግራም እንደማይበልጥ አንስተው ከዘመናዊ ቀፎ ግን ከ35 ኪሎ ግራም በላይ ምርት እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ዘመናዊ ቀፎ የማር ምርት በብዛትና በጥራት እንዲጨምር ማስቻሉን ጠቅሰው ባለፉት ዘጠኝ ወራት 1 ነጥብ 9 ሚሊየን ዘመናዊ እና የሽግግር የንብ ቀፎ ለህብረተሰቡ መሰራጫቱን ገልጸዋል።
በሀገሪቱ በተለመደው ባህላዊ የንብ ማነብ ስራ ብዙ ምርት እንደማይገኝ በማስታወስ ምርታማነትን ለማሳደግ ለንብ አናቢዎች በስፋት ዘመናዊ የንብ ቀፎ እየተከፋፈለ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።
በተጠናከረ መንገድ እየተተገበረ በሚገኘው ዘመናዊ የንብ ማነብ ስራ ንብ አንቢዎች ከፍተኛ ገቢ እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025