
አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በሀገር አቀፍ ደረጃ 215 ሺህ ቶን ማር መመረቱን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የሌማት ትሩፋት መርኃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ ከማር ምርት ከፍተኛ ውጤት መገኘቱን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ(ዶ/ር) ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 210 ሺህ ቶን ማር ለማምረት እቅድ መያዙን አስታውሰው በአፈጻጸም ረገድ 215 ሺህ ቶን ማር በማምረት ከእቅድ በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል።
በሌማት ትሩፋት መርኃ ግብር ጥሩ ውጤት ከተገኘባቸው ምርቶች አንዱ ማር መሆኑንም አስታውቀዋል።

አፈጻጸሙን የበለጠ ለማሳደግ ባህላዊ ቀፎችን ወደ ዘመናዊ ቀፎ የመለወጥ ሥራ በስፋት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
ከአንድ ባህላዊ ቀፎ የሚገኘው ምርት ከ10 ኪሎ ግራም እንደማይበልጥ አንስተው ከዘመናዊ ቀፎ ግን ከ35 ኪሎ ግራም በላይ ምርት እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
ዘመናዊ ቀፎ የማር ምርት በብዛትና በጥራት እንዲጨምር ማስቻሉን ጠቅሰው ባለፉት ዘጠኝ ወራት 1 ነጥብ 9 ሚሊየን ዘመናዊ እና የሽግግር የንብ ቀፎ ለህብረተሰቡ መሰራጫቱን ገልጸዋል።
በሀገሪቱ በተለመደው ባህላዊ የንብ ማነብ ስራ ብዙ ምርት እንደማይገኝ በማስታወስ ምርታማነትን ለማሳደግ ለንብ አናቢዎች በስፋት ዘመናዊ የንብ ቀፎ እየተከፋፈለ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።
በተጠናከረ መንገድ እየተተገበረ በሚገኘው ዘመናዊ የንብ ማነብ ስራ ንብ አንቢዎች ከፍተኛ ገቢ እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026