የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ባለፉት ዘጠኝ ወራት 215 ሺህ ቶን ማር ተመርቷል - ግብርና ሚኒስቴር

Apr 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በሀገር አቀፍ ደረጃ 215 ሺህ ቶን ማር መመረቱን ግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

በሀገር አቀፍ ደረጃ የሌማት ትሩፋት መርኃ ግብር ከተጀመረ ወዲህ ከማር ምርት ከፍተኛ ውጤት መገኘቱን የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ፍቅሩ ረጋሳ(ዶ/ር) ተናግረዋል።

በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 210 ሺህ ቶን ማር ለማምረት እቅድ መያዙን አስታውሰው በአፈጻጸም ረገድ 215 ሺህ ቶን ማር በማምረት ከእቅድ በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል።

በሌማት ትሩፋት መርኃ ግብር ጥሩ ውጤት ከተገኘባቸው ምርቶች አንዱ ማር መሆኑንም አስታውቀዋል።


አፈጻጸሙን የበለጠ ለማሳደግ ባህላዊ ቀፎችን ወደ ዘመናዊ ቀፎ የመለወጥ ሥራ በስፋት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

ከአንድ ባህላዊ ቀፎ የሚገኘው ምርት ከ10 ኪሎ ግራም እንደማይበልጥ አንስተው ከዘመናዊ ቀፎ ግን ከ35 ኪሎ ግራም በላይ ምርት እንደሚገኝ ጠቁመዋል።

ዘመናዊ ቀፎ የማር ምርት በብዛትና በጥራት እንዲጨምር ማስቻሉን ጠቅሰው ባለፉት ዘጠኝ ወራት 1 ነጥብ 9 ሚሊየን ዘመናዊ እና የሽግግር የንብ ቀፎ ለህብረተሰቡ መሰራጫቱን ገልጸዋል።

በሀገሪቱ በተለመደው ባህላዊ የንብ ማነብ ስራ ብዙ ምርት እንደማይገኝ በማስታወስ ምርታማነትን ለማሳደግ ለንብ አናቢዎች በስፋት ዘመናዊ የንብ ቀፎ እየተከፋፈለ እንደሚገኝም አስታውቀዋል።

በተጠናከረ መንገድ እየተተገበረ በሚገኘው ዘመናዊ የንብ ማነብ ስራ ንብ አንቢዎች ከፍተኛ ገቢ እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025