አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና ከዚያም በላይ አፈጻጸም እያስመዘገቡ መሆኑን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር) ገለጹ።
የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት የ2017 በጀት ዓመት የሦስተኛው ሩብ ዓመት የ100 ቀናትና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ትግበራ የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ግምገማ ተካሂዷል።
የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፥ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም መስኮች ከዕቅድ በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን አብራርተዋል።
አጠቃላይ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚሳካም የተመዘገቡ ውጤቶች አመላካች መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ፥ በመስኖ ልማት ዘርፍም አመርቂ አፈጻጸም መኖሩን ጠቅሰዋል።
ከሀገራዊ ለውጡ በፊት የመስኖ ፕሮጀክቶች ለረጅም ጊዜ በመጓተት በህብረተሰቡ በኩል ቅሬታ ሲያስነሱ እንደነበር ገልጸው፤ የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በጣም ደካማ የነበረ መሆኑን አስታውሰዋል።
በሪፎርሙም የፕሮጀክት አፈጻጸምና አስተዳደርን በማሻሻል ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ጠቅሰው፥ በበጀት ዓመቱ የመስኖ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ዕቅድና ከዚያም በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል።
በዚህ ዓመት የሚጠናቀቁ የመስኖ ግድቦችን በፍጥነት እውን በማድረግ ወደ ሥራ መግባታቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ፥ ለአብነትም የጎዴ የመስኖ ፕሮጀክትን ጠቅሰዋል።
የወልመል መስኖ ልማት ፕሮጀክት በሚቀጥለው ወር ተመርቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ በማንሳት፥ የከሰም ግድብ ፕሮጀክትንም ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።
በቀጣይ የተመዘገበውነ ስኬት በማጠናከር ለላቀ ውጤት እንተጋለን ሲሉም ነው ሚኒስትሩ በአጽንኦት የተናገሩት።
የፌደራል መንግሥት ትላልቅ የመስኖ ፕሮጀክቶችን እየገነባ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ ፕሮጀክቶች እንዳይጎዱና እንዳይስተጓጎሉ ክልሎችና ማህበረሰቡ በባለቤትነት በቅንጅት መስራት አለባቸው ብለዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025