የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ዕቅድ በፍጥነት እየተከናወኑ ነው - ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)

Apr 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና ከዚያም በላይ አፈጻጸም እያስመዘገቡ መሆኑን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር) ገለጹ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት የ2017 በጀት ዓመት የሦስተኛው ሩብ ዓመት የ100 ቀናትና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ትግበራ የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ግምገማ ተካሂዷል።

የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፥ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም መስኮች ከዕቅድ በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን አብራርተዋል።

አጠቃላይ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚሳካም የተመዘገቡ ውጤቶች አመላካች መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ፥ በመስኖ ልማት ዘርፍም አመርቂ አፈጻጸም መኖሩን ጠቅሰዋል።

ከሀገራዊ ለውጡ በፊት የመስኖ ፕሮጀክቶች ለረጅም ጊዜ በመጓተት በህብረተሰቡ በኩል ቅሬታ ሲያስነሱ እንደነበር ገልጸው፤ የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በጣም ደካማ የነበረ መሆኑን አስታውሰዋል።

በሪፎርሙም የፕሮጀክት አፈጻጸምና አስተዳደርን በማሻሻል ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ጠቅሰው፥ በበጀት ዓመቱ የመስኖ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ዕቅድና ከዚያም በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል።

በዚህ ዓመት የሚጠናቀቁ የመስኖ ግድቦችን በፍጥነት እውን በማድረግ ወደ ሥራ መግባታቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ፥ ለአብነትም የጎዴ የመስኖ ፕሮጀክትን ጠቅሰዋል።

የወልመል መስኖ ልማት ፕሮጀክት በሚቀጥለው ወር ተመርቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ በማንሳት፥ የከሰም ግድብ ፕሮጀክትንም ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቀጣይ የተመዘገበውነ ስኬት በማጠናከር ለላቀ ውጤት እንተጋለን ሲሉም ነው ሚኒስትሩ በአጽንኦት የተናገሩት።

የፌደራል መንግሥት ትላልቅ የመስኖ ፕሮጀክቶችን እየገነባ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ ፕሮጀክቶች እንዳይጎዱና እንዳይስተጓጎሉ ክልሎችና ማህበረሰቡ በባለቤትነት በቅንጅት መስራት አለባቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025