የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ዕቅድ በፍጥነት እየተከናወኑ ነው - ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)

Apr 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና ከዚያም በላይ አፈጻጸም እያስመዘገቡ መሆኑን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር) ገለጹ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት የ2017 በጀት ዓመት የሦስተኛው ሩብ ዓመት የ100 ቀናትና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ትግበራ የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ግምገማ ተካሂዷል።

የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፥ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም መስኮች ከዕቅድ በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን አብራርተዋል።

አጠቃላይ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚሳካም የተመዘገቡ ውጤቶች አመላካች መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ፥ በመስኖ ልማት ዘርፍም አመርቂ አፈጻጸም መኖሩን ጠቅሰዋል።

ከሀገራዊ ለውጡ በፊት የመስኖ ፕሮጀክቶች ለረጅም ጊዜ በመጓተት በህብረተሰቡ በኩል ቅሬታ ሲያስነሱ እንደነበር ገልጸው፤ የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በጣም ደካማ የነበረ መሆኑን አስታውሰዋል።

በሪፎርሙም የፕሮጀክት አፈጻጸምና አስተዳደርን በማሻሻል ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ጠቅሰው፥ በበጀት ዓመቱ የመስኖ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ዕቅድና ከዚያም በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል።

በዚህ ዓመት የሚጠናቀቁ የመስኖ ግድቦችን በፍጥነት እውን በማድረግ ወደ ሥራ መግባታቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ፥ ለአብነትም የጎዴ የመስኖ ፕሮጀክትን ጠቅሰዋል።

የወልመል መስኖ ልማት ፕሮጀክት በሚቀጥለው ወር ተመርቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ በማንሳት፥ የከሰም ግድብ ፕሮጀክትንም ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቀጣይ የተመዘገበውነ ስኬት በማጠናከር ለላቀ ውጤት እንተጋለን ሲሉም ነው ሚኒስትሩ በአጽንኦት የተናገሩት።

የፌደራል መንግሥት ትላልቅ የመስኖ ፕሮጀክቶችን እየገነባ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ ፕሮጀክቶች እንዳይጎዱና እንዳይስተጓጎሉ ክልሎችና ማህበረሰቡ በባለቤትነት በቅንጅት መስራት አለባቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026