የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ዕቅድ በፍጥነት እየተከናወኑ ነው - ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)

Apr 15, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 6/2017(ኢዜአ)፦ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የመስኖ ልማት ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ጊዜና ከዚያም በላይ አፈጻጸም እያስመዘገቡ መሆኑን የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር) ገለጹ።

የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በተገኙበት የ2017 በጀት ዓመት የሦስተኛው ሩብ ዓመት የ100 ቀናትና የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ትግበራ የዘጠኝ ወራት አፈፃፀም ግምገማ ተካሂዷል።

የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር አብርሃም በላይ(ዶ/ር)፥ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም መስኮች ከዕቅድ በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን አብራርተዋል።

አጠቃላይ ሀገራዊ የኢኮኖሚ ዕድገት እንደሚሳካም የተመዘገቡ ውጤቶች አመላካች መሆናቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ፥ በመስኖ ልማት ዘርፍም አመርቂ አፈጻጸም መኖሩን ጠቅሰዋል።

ከሀገራዊ ለውጡ በፊት የመስኖ ፕሮጀክቶች ለረጅም ጊዜ በመጓተት በህብረተሰቡ በኩል ቅሬታ ሲያስነሱ እንደነበር ገልጸው፤ የፕሮጀክቶች አፈጻጸም በጣም ደካማ የነበረ መሆኑን አስታውሰዋል።

በሪፎርሙም የፕሮጀክት አፈጻጸምና አስተዳደርን በማሻሻል ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን ጠቅሰው፥ በበጀት ዓመቱ የመስኖ ፕሮጀክቶች በተያዘላቸው ዕቅድና ከዚያም በላይ አፈጻጸም መመዝገቡን ገልጸዋል።

በዚህ ዓመት የሚጠናቀቁ የመስኖ ግድቦችን በፍጥነት እውን በማድረግ ወደ ሥራ መግባታቸውን የገለጹት ሚኒስትሩ፥ ለአብነትም የጎዴ የመስኖ ፕሮጀክትን ጠቅሰዋል።

የወልመል መስኖ ልማት ፕሮጀክት በሚቀጥለው ወር ተመርቆ ወደ ሥራ እንደሚገባ በማንሳት፥ የከሰም ግድብ ፕሮጀክትንም ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ብለዋል።

በቀጣይ የተመዘገበውነ ስኬት በማጠናከር ለላቀ ውጤት እንተጋለን ሲሉም ነው ሚኒስትሩ በአጽንኦት የተናገሩት።

የፌደራል መንግሥት ትላልቅ የመስኖ ፕሮጀክቶችን እየገነባ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ ፕሮጀክቶች እንዳይጎዱና እንዳይስተጓጎሉ ክልሎችና ማህበረሰቡ በባለቤትነት በቅንጅት መስራት አለባቸው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026