የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ ተጨባጭ ለውጥ እያመጣች ነው - ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር)

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 8/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የጀመረችው ሪፎርም በዓለም አቀፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን መመዘኛ የተሻለ ደረጃ ላይ እንድትገኝ ማስቻሉን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ።

የፕላንና ልማት ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሚኒስትሮች፣ የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች በተገኙበት እየተገመገመ ነው።

የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ የለውጡ መንግስት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ጨምሮ በርካታ የሪፎርም ስራዎችን ተግብሯል።


በዚህም የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ባለፉት ሰባት ዓመታት በተከታታይ ከፍተኛ ዕድገት ማስመዝገቡን አንስተዋል።

የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራ በርካታ ውጤቶችን እያስገኘ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ ዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

ለአብነትም የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርምና ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በመተግበር ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን አንስተዋል።

አካታች ዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

እነዚህ ስራዎች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን መመዘኛ የተሻለ ደረጃ ላይ እንድትገኝ አስችለዋል ነው ያሉት።


የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ስዩም መኮንን በበኩላቸው ባለፉት ሰባት ዓመታት በርካታ የሪፎርም ሥራዎችን በማከናወን አስደናቂ ውጤቶችን ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል።

በመድረኩ ያለፉት ዘጠኝ ወራት አፈጻጸምን በመገምገም በቀጣይ ሦስት ወራት በትኩረት የሚሠሩ ተግባራት ላይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025