አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 8/2017(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታ የጀመረችው ሪፎርም በዓለም አቀፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን መመዘኛ የተሻለ ደረጃ ላይ እንድትገኝ ማስቻሉን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) ገለጹ።
የፕላንና ልማት ሚኒስቴር የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ሚኒስትሮች፣ የተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሠራተኞች በተገኙበት እየተገመገመ ነው።
የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ የለውጡ መንግስት የዲጂታል ኢኮኖሚ ግንባታን ጨምሮ በርካታ የሪፎርም ስራዎችን ተግብሯል።
በዚህም የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ባለፉት ሰባት ዓመታት በተከታታይ ከፍተኛ ዕድገት ማስመዝገቡን አንስተዋል።
የተሟላ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፖሊሲ ትግበራ በርካታ ውጤቶችን እያስገኘ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ ዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።
ለአብነትም የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ሪፎርምና ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ስትራቴጂን በመተግበር ተጨባጭ ለውጥ መምጣቱን አንስተዋል።
አካታች ዲጂታል ኢኮኖሚ ለመገንባት የ5 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ኮደርስ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።
እነዚህ ስራዎች ኢትዮጵያን በዓለም አቀፍ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን መመዘኛ የተሻለ ደረጃ ላይ እንድትገኝ አስችለዋል ነው ያሉት።
የፕላንና ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ስዩም መኮንን በበኩላቸው ባለፉት ሰባት ዓመታት በርካታ የሪፎርም ሥራዎችን በማከናወን አስደናቂ ውጤቶችን ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል።
በመድረኩ ያለፉት ዘጠኝ ወራት አፈጻጸምን በመገምገም በቀጣይ ሦስት ወራት በትኩረት የሚሠሩ ተግባራት ላይ አቅጣጫ እንደሚቀመጥ ጠቁመዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025