የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ የአምራች ኢንዱስትሪውን የውጭ ምንዛሪ እና የፋይናንስ አቅርቦት በማሻሻል የዘርፉን አፈፃፀም አሳድጎታል-ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 9/2017 (ኢዜአ)፡-የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ የአምራች ኢንዱስትሪውን የውጭ ምንዛሪ እና የፋይናንስ አቅርቦት በማሻሻል የዘርፉን አፈፃፀም ማሳደግ ማስቻሉን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ገለጸ፡፡


በኢትዮጵያ ከለውጡ ወዲህ በተደረጉ ሀገራዊ የሪፎርም ሥራዎች ሁሉን አቀፍ እድገትና ብልጽግናን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ውጤቶች ተመዝግበዋል፡፡


ከሃምሌ ወር 2016 ዓ.ም ጀምሮ ገቢራዊ የተደረገው የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያው ኢኮኖሚውን በማነቃቃት ተጨባጭ ለውጦችን ማሳየት ጀምሯል፡፡


የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው በኋላ የአምራች ኢንዱስትሪው ውጤታማነት እየተሻሻለ መጥቷል፡፡


ተዘግተው የነበሩ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ምርት በማስገባት እና የማምረት አቅማቸውን በማሳደግ አቅማቸውን እንዲያሻሽሉ ማድረግ መቻሉንም ገልጸዋል፡፡


ከዚህ በፊት የአምራች ኢንዱስትሪው ትልቁ ማነቆ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደነበር አስታውሰው፤ ሪፎርሙ በቂ የውጭ ምንዛሪ አቅርቦት በመፍጠር የተሻለ የግብዓት አቅርቦት ማግኘት እንዲችሉ አድርጓል ብለዋል፡፡


በዚህም ከሪፎርሙ በኋላ በተደረገ የጋራ ርብርብ የአምራች ኢንዱስትሪዎችን የማምረት አቅም ከ60 በመቶ በላይ ማሳደግ መቻሉን ገልጸዋል፡፡


መንግሥት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን ለመቀነስ ተኪ ምርቶች ላይ በትኩረት እየሰራ መሆኑን ገልጸው፤ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 3 ቢሊዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው ተኪ ምርት ተገኝቷል ብለዋል፡፡


የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የተኪ ምርት ስትራቴጂው ውጤታማ እንዲሆን ያስቻለ ለመሆኑ ማሳያ ነው ብለዋል፡፡


በአዲስ አበባ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ለተለያዩ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች የሚውሉት የኤሌክትሪክ ምሰሶዎች፣ ገመዶች እና ትራንስፎርመሮች በሀገር ውስጥ የሚመረቱ መሆናቸውንም ገልጸዋል።


አምራች ኢንዱስትሪው ምርቶችን ለውጭ ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ማሳደግ እንደሚጠበቅባቸው ተናግረው፥ ዘርፉ በተያዘው በጀት አመት 276 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማስገኘቱን ተናግረዋል፡፡


ይሄውም ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ18 በመቶ ብልጫ እንዳለው ጠቅሰው፤ ከሀገሪቱ አቅም አንፃር ብዙ መስራት ይጠበቅብናል ብለዋል።


መንግሥት የአምራች ኢንዱስትሪዎች የፋይናንስ አቅርቦት ችግር ለመፍታት 76 በመቶ ብድር ለግሉ ዘርፍ እንዲሄድ ማድረጉን ገልጸዋል፡፡


የዘርፉ የማምረት አቅም በመሻሻሉ እና ተጨማሪ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ኢንቨስትመንት መሳብ በመቻሉ ከፍተኛ የሥራ እድል ተፈጥሯል ብለዋል፡፡


የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ለአምራች ኢንዱስትሪ ምቹ ከባቢ መፍጠሩን ገልጸው፤ ዘርፉ የሚጠበቅበትን 12 በመቶ እድገት ማሳካት የሚያስችለውን አቅም ፈጥሯል ብለዋል፡፡


መንግስት የአምራች ኢንዱስትሪውን ለማበረታታት ከሚሰጠው የታክስ እፎይታ በተጨማሪ አዲስ የኢንቨስትመንት ስትራቴጂ እየተዘጋጀ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026