
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 9/2017(ኢዜአ):-በስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በትኩረት እንደሚሰራ የሐረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለፁ።
የሀረሪ ክልል ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ በቀጣይ አራት ወራት በሚካሄደው የስራ እድል ፈጠራ ንቅናቄ እቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይተዋል ።

በመርሀ-ግብሩ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ በክልሉ በስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል።
በክልሉ የሚገኙ ስራ አጥ ዜጎችን ለይቶ ስልጠናዎችን በመስጠት፤በአካባቢው ላይ ያሉ ፀጋዎችን በመጠቀም ተደራጅተው ወደ ስራ እንዲገቡ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ሰራዎች በቀጣይ ጊዜያትም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ርብርብ ይደረጋል።
በተለይ ገበያ ላይ ተፈላጊ የሆኑ የክህሎት ስልጠናዎችን ከመስጠት ጀምሮ የዜጎችን የስራ ባህል በማሳደግ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነታቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ እተሰራ እንደሚገኝ ነው የጠቆሙት።
የኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ አቶ እስማኢል ዩሱፍ በበኩላቸው፥ ዜጎች ዕራሳቸውን በኢኮኖሚ ከመቻል በዘለለ አምራች እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ትኩረት ተሰቶ አጫጭር ክህሎት መር ስልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑን ገልፀዋል።
በቀጣይ አራት ወራት ለስራ አጥ ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር 50 ሚሊዮን ብር ተመድቦ ወደ ስራ መገባቱን አቶ እስሚኢል መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026