
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 9/2017(ኢዜአ):-በስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በትኩረት እንደሚሰራ የሐረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለፁ።
የሀረሪ ክልል ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ በቀጣይ አራት ወራት በሚካሄደው የስራ እድል ፈጠራ ንቅናቄ እቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይተዋል ።

በመርሀ-ግብሩ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ በክልሉ በስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል።
በክልሉ የሚገኙ ስራ አጥ ዜጎችን ለይቶ ስልጠናዎችን በመስጠት፤በአካባቢው ላይ ያሉ ፀጋዎችን በመጠቀም ተደራጅተው ወደ ስራ እንዲገቡ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ሰራዎች በቀጣይ ጊዜያትም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ርብርብ ይደረጋል።
በተለይ ገበያ ላይ ተፈላጊ የሆኑ የክህሎት ስልጠናዎችን ከመስጠት ጀምሮ የዜጎችን የስራ ባህል በማሳደግ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነታቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ እተሰራ እንደሚገኝ ነው የጠቆሙት።
የኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ አቶ እስማኢል ዩሱፍ በበኩላቸው፥ ዜጎች ዕራሳቸውን በኢኮኖሚ ከመቻል በዘለለ አምራች እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ትኩረት ተሰቶ አጫጭር ክህሎት መር ስልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑን ገልፀዋል።
በቀጣይ አራት ወራት ለስራ አጥ ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር 50 ሚሊዮን ብር ተመድቦ ወደ ስራ መገባቱን አቶ እስሚኢል መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026