የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በትኩረት ይሰራል

Apr 18, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 9/2017(ኢዜአ):-በስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በትኩረት እንደሚሰራ የሐረሪ ክልል ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ ገለፁ።

የሀረሪ ክልል ኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ በቀጣይ አራት ወራት በሚካሄደው የስራ እድል ፈጠራ ንቅናቄ እቅድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይተዋል ።


በመርሀ-ግብሩ ላይ የተገኙት በብልፅግና ፓርቲ የሐረሪ ክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ጌቱ ወዬሳ በክልሉ በስራ ዕድል ፈጠራ የዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማጎልበት በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀዋል።

በክልሉ የሚገኙ ስራ አጥ ዜጎችን ለይቶ ስልጠናዎችን በመስጠት፤በአካባቢው ላይ ያሉ ፀጋዎችን በመጠቀም ተደራጅተው ወደ ስራ እንዲገቡ ለማድረግ እየተሰሩ ያሉ ሰራዎች በቀጣይ ጊዜያትም ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ርብርብ ይደረጋል።

በተለይ ገበያ ላይ ተፈላጊ የሆኑ የክህሎት ስልጠናዎችን ከመስጠት ጀምሮ የዜጎችን የስራ ባህል በማሳደግ ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተጠቃሚነታቸውን በዘላቂነት ለማረጋገጥ እተሰራ እንደሚገኝ ነው የጠቆሙት።

የኢንተርፕራይዝ ልማትና ኢንዱስትሪ ቢሮ ሃላፊ አቶ እስማኢል ዩሱፍ በበኩላቸው፥ ዜጎች ዕራሳቸውን በኢኮኖሚ ከመቻል በዘለለ አምራች እና ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ለማስቻል ትኩረት ተሰቶ አጫጭር ክህሎት መር ስልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑን ገልፀዋል።

በቀጣይ አራት ወራት ለስራ አጥ ዜጎች የስራ ዕድል ለመፍጠር 50 ሚሊዮን ብር ተመድቦ ወደ ስራ መገባቱን አቶ እስሚኢል መግለጻቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን የተገኘ መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026