ባህርዳር ፤ ሚያዚያ 10/2017 (ኢዜአ)፡- በባህርዳር ከተማ በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ማምሻውን በከፍተኛ አመራር አባላት ተጎበኘ።
የኮሪደር ልማቱ አካል የሆነው የሞባይልና ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶችን ቻርጅ ማድረግ የሚያስችለው ስማርት ፖል ተከላና የማብራት የሙከራ ትግበራ ተከናውኗል።
የአረንጓዴ ልማት፣ የእግረኛና የብስክሌት መንገድና ሌሎች መዝናኛዎችን በማካተት የተገነባው የሶስት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት የመብራቱ መጀመር የከተማዋን ድምቀት የሚጨምር መሆኑ ተመልክቷል።
ማምሻውን ልማቱን የጎበኙት በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንደላማው የሚመራ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራር አባላት ናቸው።
የከተማ አስተዳደሩ የኮሪደር ልማቱ አካል የሆነውን ከአልማ ህንጻ ፊት ለፊት ዋተር ፍሮንት የሚደርሰው የ800 ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታ ሰሞኑን ማስጀመሩን በወቅቱ ዘግበናል።
የባህርዳር ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ምዕራፎች የ22 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ለማካሄድ እየሰራ እንደሚገኝ ከከተማ አስተዳደሩ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025