
ባህርዳር ፤ ሚያዚያ 10/2017 (ኢዜአ)፡- በባህርዳር ከተማ በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ማምሻውን በከፍተኛ አመራር አባላት ተጎበኘ።
የኮሪደር ልማቱ አካል የሆነው የሞባይልና ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶችን ቻርጅ ማድረግ የሚያስችለው ስማርት ፖል ተከላና የማብራት የሙከራ ትግበራ ተከናውኗል።
የአረንጓዴ ልማት፣ የእግረኛና የብስክሌት መንገድና ሌሎች መዝናኛዎችን በማካተት የተገነባው የሶስት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት የመብራቱ መጀመር የከተማዋን ድምቀት የሚጨምር መሆኑ ተመልክቷል።

ማምሻውን ልማቱን የጎበኙት በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንደላማው የሚመራ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራር አባላት ናቸው።
የከተማ አስተዳደሩ የኮሪደር ልማቱ አካል የሆነውን ከአልማ ህንጻ ፊት ለፊት ዋተር ፍሮንት የሚደርሰው የ800 ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታ ሰሞኑን ማስጀመሩን በወቅቱ ዘግበናል።
የባህርዳር ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ምዕራፎች የ22 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ለማካሄድ እየሰራ እንደሚገኝ ከከተማ አስተዳደሩ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026