
ባህርዳር ፤ ሚያዚያ 10/2017 (ኢዜአ)፡- በባህርዳር ከተማ በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ የሚገኘው የኮሪደር ልማት ማምሻውን በከፍተኛ አመራር አባላት ተጎበኘ።
የኮሪደር ልማቱ አካል የሆነው የሞባይልና ሌሎች የኤሌክትሮኒክስ ቁሳቁሶችን ቻርጅ ማድረግ የሚያስችለው ስማርት ፖል ተከላና የማብራት የሙከራ ትግበራ ተከናውኗል።
የአረንጓዴ ልማት፣ የእግረኛና የብስክሌት መንገድና ሌሎች መዝናኛዎችን በማካተት የተገነባው የሶስት ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት የመብራቱ መጀመር የከተማዋን ድምቀት የሚጨምር መሆኑ ተመልክቷል።

ማምሻውን ልማቱን የጎበኙት በባህርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንደላማው የሚመራ የከተማ አስተዳደሩ ከፍተኛ አመራር አባላት ናቸው።
የከተማ አስተዳደሩ የኮሪደር ልማቱ አካል የሆነውን ከአልማ ህንጻ ፊት ለፊት ዋተር ፍሮንት የሚደርሰው የ800 ሜትር የአስፋልት መንገድ ግንባታ ሰሞኑን ማስጀመሩን በወቅቱ ዘግበናል።
የባህርዳር ከተማ አስተዳደር በተለያዩ ምዕራፎች የ22 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት ለማካሄድ እየሰራ እንደሚገኝ ከከተማ አስተዳደሩ የተገኘው መረጃ ያሳያል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026