የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በሐረሪ ክልል 33 የካፒታል ፕሮጀክቶች ተጠናቀው አገልግሎት እየሰጡ ናቸው

Apr 23, 2025

IDOPRESS

ሐረር፣ ሚያዝያ 14/2017(ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የመለሱ 33 የተለያዩ ፕሮጀክቶች ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት መጀመራቸውን የሐረሪ ክልል ፕላን ኮሚሽን ገለጸ።

በሐረሪ ክልል የዘንድሮ የዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ርዕሰ መስተዳድሩ ኦርዲን በድሪ በተገኙበት እየተገመገመ ነው።


በግምገማው ላይ የክልሉ የፕላን ኮሚሽነር ኢብሳ ኢብራሂም የክልሉን የካፒታል ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ሪፖርት አቅርበዋል።

ኮሚሽነሩ በወቅቱ እንደተናገሩት፤ በዘጠኙ ወራት የገጠርና የከተማውን ማህበረሰብ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች የመለሱ 33 ፕሮጀክቶች ተጠናቀዋል።

አገልግሎት እየሰጡ ከሚገኙት መካከል የከተማው የኮሪደር ልማት፣ የመንገድ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ የትምህርት እና ሌሎች ፕሮጀክቶች ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።


በተጨማሪም ለህብረተሰቡ ፈጣንና ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ የተቋማት ዕድሳትና ግንባታ፣ የዲጂታል ቴክኖሎጂ መሠረተ ልማቶች ዝርጋታዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።

በክልሉ ዘንድሮ በመተግበር ላይ ከሚገኙት 27 ነባርና 57 አዳዲስ ፕሮጀክቶች መካከል ደግሞ 39ኙ ከ60 እስከ 95 በመቶ የተጠናቀቁ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

በቀሪ የበጀት ወራት እነዚህን በተቀናጀ መንገድ በማጠናቀቅ የህዝብን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች በላቀ ደረጃ ለመመለስ መረባረብ ይገባል ብለዋል።

የግምገማው መድረኩ ቀጥሎ በአሁኑ ሰዓት የክልሉ ገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ቢሮ ኃላፊ አቶ መሐመድ ያህያ ክልሉ የሚያመነጨውን ያህል ገቢ ለመሰበሰብና የክልሉን ህዝብ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመፍታት ባለፉት ዘጠኝ የበጀት ወራት የተሰሩ ስራዎችን ሪፖርት እያቀረቡ ይገኛሉ።

የበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት የስራ አፈፃፀም ግምገማውን ርዕሰ መስተዳደሩ ኦርዲን በድሪ እየመሩት ሲሆን የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች፣ የየወረዳዎቹ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳታፊ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026