
መቀሌ፤ ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፦ በትግራይ ክልል የታዳጊዎችን የቁጠባ ባህል በማሳደግ በቀጣይ የተሻለ ህይወት መምራት የሚያስችሉ አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑ ተገለጸ።
የክልሉ የገበሬዎች የቁጠባና ብድር የህብረት ስራ ማህበራት ታዳጊ ህጻናት የቁጠባ ልምድን እንዲያዳብሩ ከወላጆቻቸው ጋር በተደረገ ጥረት እስካሁን 38 ሚሊዮን ብር መቆጠብ እንደተቻለም ተመልክቷል።
አዲሱን ትውልድ በቁጠባ ባህል ኮትኩቶ ማሳደግ የወደፊት ህይወቱን የተሻለ እንዲሆን ዕድሉን ሊያሰፋ እንደሚችል እሙን ነው።
የታዳጊዎችን የቁጠባ ባህልን በማሳደግ በቀጣይ የተሻለ ህይወት መምራት የሚያስችሉ አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ ሲሆን በዚህም ወላጆችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት እገዛ ወሳኝ መሆኑ ይታመናል።
በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የህብረት ስራ ማህበራት ኤጀንሲ ምክትል ኃላፊ አቶ የማነ ገብረመስቀል፤ የቁጠባ ባህልን ማሳደግ ለምጣኔ ሃብት እድገት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።
በዚህ ረገድ በተለይም የወጣቶችና የታዳጊዎች የቁጠባ ባህል እያደገ እንዲሄድና የወደፊት ህይወታቸውን በተሻለ መልኩ መምራት እንዲችሉ መስራት ይገባል ብለዋል።

በተለያዩ አካባቢዎች የአርሶ አደሮች ልጆች ላይ ትኩረት በማድረግ እንዲቆጥቡ በማድረግ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 83 ሺህ ታዳጊዎች 38 ሚሊዮን ብር እንዲቆጥቡ ተደርጓል ነው ያሉት።
የታዳጊዎቹ የቁጠባ ልምድ ለቀጣይ ህይወታቸው ጥሩ መሰረት የሚያስይዝ መሆኑን ጠቅሰው በሁሉም አካባቢዎች ልምድ ሆኖ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።
ታዳጊዎቹ ከልጅነታቸው ጀምሮ የቁጠባ ባህልን ትርጉምና አስፈላጊነት እንዲገነዘቡ ተከታታይ የግንዛቤ ትምህርት የሚያስፈልጋቸው መሆኑንም አንስተዋል።
በክልሉ ከ500 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ባለፉት ዘጠኝ ወራት 1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በመቆጠብ የሚያስፈልጋቸውን የግብርና ግብዓት በቀላሉ ለመግዛት መቻላቸውም ታውቋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026