የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በክልሉ የታዳጊዎችን የቁጠባ ባህል በማሳደግ በቀጣይ የተሻለ ህይወት መምራት የሚያስችሉ አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ ነው 

Apr 23, 2025

IDOPRESS

መቀሌ፤ ሚያዚያ 14/2017(ኢዜአ)፦ በትግራይ ክልል የታዳጊዎችን የቁጠባ ባህል በማሳደግ በቀጣይ የተሻለ ህይወት መምራት የሚያስችሉ አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ መሆኑ ተገለጸ።

የክልሉ የገበሬዎች የቁጠባና ብድር የህብረት ስራ ማህበራት ታዳጊ ህጻናት የቁጠባ ልምድን እንዲያዳብሩ ከወላጆቻቸው ጋር በተደረገ ጥረት እስካሁን 38 ሚሊዮን ብር መቆጠብ እንደተቻለም ተመልክቷል።

አዲሱን ትውልድ በቁጠባ ባህል ኮትኩቶ ማሳደግ የወደፊት ህይወቱን የተሻለ እንዲሆን ዕድሉን ሊያሰፋ እንደሚችል እሙን ነው።

የታዳጊዎችን የቁጠባ ባህልን በማሳደግ በቀጣይ የተሻለ ህይወት መምራት የሚያስችሉ አሰራሮች ተግባራዊ እየተደረጉ ሲሆን በዚህም ወላጆችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት እገዛ ወሳኝ መሆኑ ይታመናል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው በትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የእርሻና ተፈጥሮ ሃብት ቢሮ የህብረት ስራ ማህበራት ኤጀንሲ ምክትል ኃላፊ አቶ የማነ ገብረመስቀል፤ የቁጠባ ባህልን ማሳደግ ለምጣኔ ሃብት እድገት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

በዚህ ረገድ በተለይም የወጣቶችና የታዳጊዎች የቁጠባ ባህል እያደገ እንዲሄድና የወደፊት ህይወታቸውን በተሻለ መልኩ መምራት እንዲችሉ መስራት ይገባል ብለዋል።


በተለያዩ አካባቢዎች የአርሶ አደሮች ልጆች ላይ ትኩረት በማድረግ እንዲቆጥቡ በማድረግ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 83 ሺህ ታዳጊዎች 38 ሚሊዮን ብር እንዲቆጥቡ ተደርጓል ነው ያሉት።

የታዳጊዎቹ የቁጠባ ልምድ ለቀጣይ ህይወታቸው ጥሩ መሰረት የሚያስይዝ መሆኑን ጠቅሰው በሁሉም አካባቢዎች ልምድ ሆኖ መቀጠል እንዳለበት አስገንዝበዋል።

ታዳጊዎቹ ከልጅነታቸው ጀምሮ የቁጠባ ባህልን ትርጉምና አስፈላጊነት እንዲገነዘቡ ተከታታይ የግንዛቤ ትምህርት የሚያስፈልጋቸው መሆኑንም አንስተዋል።

በክልሉ ከ500 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ባለፉት ዘጠኝ ወራት 1 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በመቆጠብ የሚያስፈልጋቸውን የግብርና ግብዓት በቀላሉ ለመግዛት መቻላቸውም ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025