የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የቴክኖሎጂና የክህሎት ውድድሩ የንድፈ ሀሳብ እውቀቶችን ወደ ተግባር ለመለወጥ ያግዛል - የውድድሩ ተሳታፊዎች

Apr 24, 2025

IDOPRESS

ወላይታ ሶዶ፤ ሚያዚያ 15/2017(ኢዜአ)፦ ክልል አቀፍ የቴክኖሎጂ፣ የክህሎት እና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር በንድፈ ሀሳብ ያገኙትን እውቀት ወደ ተግባር ለመቀየር እንደሚያግዛቸው የውድድሩ ተሳታፊዎች ገለጹ።

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ "ብሩህ አዕምሮዎች በክህሎት የበቁ ዜጎች" በሚል መሪ ሀሳብ ያዘጋጀው ክልል አቀፍ የቴክኖሎጂ፣ የክህሎትና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድር በወላይታ ሶዶ እና በአርባ ምንጭ ከተሞች እየተካሄደ ነው።

በወላይታ ሶዶ ከተማ በተጀመረው ውድድር ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የውድድሩ ተሳታፊዎች እንደገለጹት የውድድሩ መዘጋጀት በኮሌጆች ያገኙትን የንድፈ ሀሳብ ዕውቀት ወደ ተግባር ለመቀየርና ልምድ በማዳበር የበለጠ ለመስራት የሚያግዛቸው ነው።


በቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የሚሰጡ ስልጠናዎች ከቴክኖሎጂ ጋር በመላመድና ምርታማ በመሆን የኢኮኖሚና ማህበራዊ ችግሮቻችን በራስ አቅም መፍታት የሚያስችሉ መሆናቸውንም ነው የተናገሩት።


ከሳውላ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአትክልትና ፍራፍሬ ማቀነባበሪያ ቴክኖሎጂ የፈጠራ ውጤትን ይዞ የቀረበው ተወዳዳሪ ተመስገን አዝማች ክልላዊ ውድድር መዘጋጀቱ በኮሌጅ ያገኘነውን የንድፈ ሀሳብ ዕውቀት ወደ ተግባር በመቀየር ይበልጥ ተጠቃሚ እንድንሆን ያስችለናል ብሏል።

በቴክኖሎጂ በመታገዝ ተኪ ምርቶችን በስፋት በማምረት የህብረተሰቡን ፍላጎት ለማሟላት ትልቅ መነሳሳት የሚፈጥር መሆኑንም ነው የተናገረው።

ውድድሩ ከጠባቂነት አስተሳሰብ ወጥቶ በራስ ጥረት ሠርቶ ለመለወጥ የሚያነሳሳ ነው ያለችው ደግሞ ከዲላ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በምግብ አዘገጃጀት ክህሎት የተወዳደረችው ፍጹም ዮሐንስ ናት።

ውድድሩ ልምድ በመለዋወጥና ክፍተቶቻችንን በማረም በቀጣይ ምርታማ ለመሆን ጉልህ አስተዋጽኦ አለው ብላለች።


የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ምክትልና የቴክኖሎጂ ሽግግርና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ዘርፍ ሃላፊ አቶ በዛብህ ገበየሁ በበኩላቸው እንዳሉት የውድድሩ መዘጋጀት ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሀገር ውስጥ ለመተካት እየተደረገ ያለውን ጥረት የሚያግዝ ነው።

በቢሮው ስር ባሉ ኮሌጆች የሚሰጠው ተግባር ተኮር ትምህርትና ስልጠና ከውጭ የሚገቡ ምርቶችን በሚተኩ ቴክኖሎጂዎች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑንም አመልክተዋል።

ከቴክኖሎጂ ማዕከላት የፈጠራ ሀሳቦችንና ቴክኖሎጂዎችን በመሰብሰብ ሰልጣኞች ስልጠናቸውን ሲጨርሱ በተናጠልም ሆነ በጋራ ቴክኖሎጂዎችን ተጠቅመው ውጤታማ እንዲሆኑ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ቴክኖሎጂዎችና የፈጠራ ሀሳቦች የማህበረሰቡን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች በመሰረታዊነት እንዲፈቱ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱንም ነው የገለጹት።

ለአራት ቀናት በሚካሄደው ክልል አቀፍ ውድድር በክህሎት ዘርፍ በ20 ሙያዎች፣ በቴክኖሎጂ ዘርፍ ደግሞ በ14 ቴክኖሎጂዎች እንዲሁም በ6 ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሥራዎች ውድድሩ እንደሚካሄድ ታውቋል።

በውድድሩ የተለያዩ አሰልጣኝ መምህራን፣ ሰልጣኞችና ኢንተርፕራይዞች በመሳተፍ ላይ ናቸው።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026