የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ሀገራችንን የመገንባት የማነጽና የማስዋብ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

Apr 24, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዚያ 15/2017(ኢዜአ)፦ ሀገርን የመገንባት የማነጽና የማስዋብ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የካዛንቺስ የኮሪደር ልማት ስራን በትላንትናው እለት መርቀዋል።

ከጥቂት ወራት በፊት ካዛንቺስ የነበረው መልክ ዛሬ ከሚታየው በእጅጉ የተራራቀና ለእይታም ሆነ ለኑሮ በብዙ መልኩ የማይመች እንደነበር አንስተዋል።

የሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት ካዛንቺስን ያካተተ ሆኖ መጀመሩን ገልጸው፤ በጥቂት ወራት ውስጥም በአካባቢው የተገኘው ውጤት በእጅጉ የሚያኮራ ስራ ነው ብለዋል።


ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከካዛንቺስ የተነሱ ወገኖች ያሉበትን ሰፈር መመልከታቸውን አስታውሰው፤ ቀደም ሲል ሲኖሩበት የነበረው ከአዲሱ የኑሮ ልምምድና የአኗኗር ዘዬ አኳያ ሲታይ በእጅጉ የተሻለ መሆኑን ገልጸዋል።

ነዋሪዎቹ አሁን ያለው ኑሯቸው የተሻለ መሆኑን ማረጋገጣቸውንም ጠቅሰዋል።

በየትኛውም ሀገር የሚታየው ዘመናዊነት፣ ለውጥና መሻሻል የሚገለጸው በዚህ መንገድ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ የዘመኑ የሚባሉ ከተሞች አረንጓዴና ንጹህ የሆኑ ከተሞች መሆናቸውን አብራርተዋል።

የከተማችን ነዋሪዎች መገንዘብ ያለባቸው ከነበርንበት አውድ ሁኔታ ወደ ሚያምረው ሁኔታ ለመውጣት እልህ አስጨራሽ ትጋት ይጠይቃል ሲሉም ገልጸዋል።

ሀገራችንን ለማሳደግና ልጆቻችን ተስፈኞች እንዲሆኑ የበለጸገች ሀገር መስራት እንዲችሉ የተከፈለ ዋጋ መሆኑንም መረዳት እንደሚገባ ተናግረዋል።


ሀገራችንን የመገንባት የማነጽ የማስዋብ ስራው ተስፋችንን፣ ህልማችንንና ንግግራችንን ወደ መሬት አውርዶ የማሳየቱ ጉዳይ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።

ለዚህም በየደረጃው ያሉ አመራሮች በትጋት በመፍጠርና በመፍጠን መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

በአሁኑ ወቅት ትጋት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፤ በትጋት አንድ ደረጃ ስንደርስ የሚቀጥለውን ማለም እንደሚያስፈልግም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026