
አርባ ምንጭ፤ ሚያዝያ 17/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዲጂታል ዓለም ተወዳዳሪ ለመሆን በቴክኖሎጂ፣ በእውቀትና በክህሎት የበቃ ዜጋን ለማፍራት በትኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ።
በክልሉ የመጀመሪያ ዙር ክልላዊ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድርና አውደ ርዕይ መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ተወካይና የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ እንደገለጹት፣ በዲጂታል ዓለም ተወዳዳሪ ለመሆን በክልሉ በቴክኖሎጂ፣ በዕውቀትና በክህሎት የበቁ ዜጎችን ለመፍጠር በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።
በክልል ደረጃ እየተካሄደ ያለው ውድድርና ዐውደ ርዕይም የተሻለ የቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎት ያላቸውን ዜጎች ከመለየት ባለፈ የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎችን ለመቅዳት እና ለማሸጋገር ሚናው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህ ረገድ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ በስሩ የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን እንዲያፈሩ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን አስረድተዋል።
የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዮት ደምሰ በበኩላቸው ውድድሩ በቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎት ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት ጠቃሚ መሆኑን ገልጸው፣ ሙያና ሙያተኞችን የማበረታታት ዓላማም እንዳለው ጠቁመዋል።
በተጨማሪም ዜጎች የሙያ ክቡርነትን ተረድተው እንደዝንባሌያቸው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማትን እንዲቀላቀሉ ለማስቻል ነው ብለዋል።
በክልሉ በ35 የስልጠና ኮሌጆች ዜጎች በቴክኖሎጂ፣ በክህሎትና በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሥራዎች እንዲበቁ በልዩ ትኩረት እየተሠራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ በዛብህ ገበየሁ ናቸው።
ሰልጣኞቹ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ አሻራቸውን ሊያኖሩ ይገባል ብለዋል።
ክህሎት መር የሥራ ዕድል በመፍጠርና ለአምራች ኢንዱስትሪው የሰው ሃይል በማቅረብ በኩል አበረታች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።
በመድረኩ የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የዘርፉ አሠልጣኞችና ሠልጣኞች እንዲሁም ኢንተርፕራይዞች ተገኝተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026