የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ በዲጂታል ዓለም ተወዳዳሪ ለመሆን በቴክኖሎጂ እውቀትና ክህሎት ብቁ ዜጋን ለማፍራት ትኩረት ተሰጥቷል

Apr 27, 2025

IDOPRESS

አርባ ምንጭ፤ ሚያዝያ 17/2017(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በዲጂታል ዓለም ተወዳዳሪ ለመሆን በቴክኖሎጂ፣ በእውቀትና በክህሎት የበቃ ዜጋን ለማፍራት በትኩረት እየተሠራ መሆኑ ተገለጸ።

በክልሉ የመጀመሪያ ዙር ክልላዊ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድርና አውደ ርዕይ መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ተወካይና የከተማና መሠረተ ልማት ቢሮ ሃላፊ አቶ ብርሃኑ ዘውዴ እንደገለጹት፣ በዲጂታል ዓለም ተወዳዳሪ ለመሆን በክልሉ በቴክኖሎጂ፣ በዕውቀትና በክህሎት የበቁ ዜጎችን ለመፍጠር በትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል።

በክልል ደረጃ እየተካሄደ ያለው ውድድርና ዐውደ ርዕይም የተሻለ የቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎት ያላቸውን ዜጎች ከመለየት ባለፈ የማህበረሰቡን ችግር የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎችን ለመቅዳት እና ለማሸጋገር ሚናው የጎላ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህ ረገድ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ በስሩ የሚገኙ የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋን እንዲያፈሩ በትኩረት ሲሰራ መቆየቱን አስረድተዋል።

የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ሃላፊ አቶ አብዮት ደምሰ በበኩላቸው ውድድሩ በቴክኖሎጂ ዕውቀትና ክህሎት ብቁ ባለሙያዎችን ለማፍራት ጠቃሚ መሆኑን ገልጸው፣ ሙያና ሙያተኞችን የማበረታታት ዓላማም እንዳለው ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ዜጎች የሙያ ክቡርነትን ተረድተው እንደዝንባሌያቸው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ተቋማትን እንዲቀላቀሉ ለማስቻል ነው ብለዋል።

በክልሉ በ35 የስልጠና ኮሌጆች ዜጎች በቴክኖሎጂ፣ በክህሎትና በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሥራዎች እንዲበቁ በልዩ ትኩረት እየተሠራ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ የክልሉ ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ቢሮ ምክትል ሃላፊ አቶ በዛብህ ገበየሁ ናቸው።

ሰልጣኞቹ የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ አሻራቸውን ሊያኖሩ ይገባል ብለዋል።

ክህሎት መር የሥራ ዕድል በመፍጠርና ለአምራች ኢንዱስትሪው የሰው ሃይል በማቅረብ በኩል አበረታች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልጸዋል።

በመድረኩ የክልልና የዞን ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች፣ የዘርፉ አሠልጣኞችና ሠልጣኞች እንዲሁም ኢንተርፕራይዞች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026