
መቱ፤ሚያዝያ 18/2017 (ኢዜአ)፦በኢሉ አባቦር ዞን 1 ሺህ 900 ሄክታር መሬት ማልማት የሚያስችሉ አነስተኛ መስኖ ግድቦች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ መስኖ ልማት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።
የኢሉ አባቦር ዞን መስኖ ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ደመቁ ተረፈ እንዳሉት፥ አነስተኛ መስኖ ግድቦች ግንባታው በሁለት ወረዳዎች እየተከናወነ ነው።
የክልሉ መንግስት 'ፊና' በተሰኘ ፕሮጀክት ውኃ አጠር በሆኑ አካባቢዎች አነስተኛና መለስተኛ የመስኖ ግድቦች ግንባታ እያካሄደ ሲሆን በዞኑ በግንባታ ላይ የሚገኙ ግድቦችም የዚሁ አካል ናቸው ብለዋል።
የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ሲጠናቀቅ የአካባቢው አርሶ አደሮችን የማምረት አቅም በማሳደግ ተጠቃሚ የሚያደርጋቸው እንደሆነ ገልጸዋል።
በሁለቱ ወረዳዎች 4 ሺህ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ማድረግ የሚችሉት እነዚሁ ግድቦች ግንባታቸው በ400 ሚሊዮን ብር ወጪ ነው እየተከናወነ የሚገኘው ብለዋል።
ግድቦቹ በሚገነቡበት አካባቢ የሚኖሩ አርሶ አደሮችም የመስኖ ግድቦቹ ከክረምት ባለፈ በበጋ ወራት ተጨማሪ የማምረት አቅም እንደሚፈጥርላቸው ተናግረዋል።
አርሶ አደር አበበ ሀብተወልድ ፕሮጀክቶቹ በአካባቢያቸው የሚገኘውን ወንዝ በግብርና ስራቸው ላይ በመጠቀም ክረምትና በጋ ማምረት የሚያስችለን ነው ብለዋል።
በዚህም ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ወደስራ ሲገባ በዝናብ ወቅት ብቻ ላይ የተመሰረተውን ግብርናቸውን በማሻሻል ዓመቱን ሙሉ ማምረት እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል።
ሌላው አቶ ጫንያለው ያደታ ደግሞ የመስኖ ግድቡ በግብርና ስራ እያከናወኗቸው ባሉ የተለያዩ ኢኒሼቲቮች ላይ ያላቸው ተሳትፎ እንዲጨምር ይረዳል ብለዋል።
በአካባቢያቸው ሌሎች የግብርና ስራዎችም ላይ ጠንክረው በመስራት ሁለንተናዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እንደሚያግዛቸው አክለዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026