የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኢሉ አባቦር ዞን 1 ሺህ 900 ሄክታር መሬት ማልማት የሚያስችሉ አነስተኛ መስኖ ግድቦች ግንባታ እየተከናወነ ነው

Apr 27, 2025

IDOPRESS

መቱ፤ሚያዝያ 18/2017 (ኢዜአ)፦በኢሉ አባቦር ዞን 1 ሺህ 900 ሄክታር መሬት ማልማት የሚያስችሉ አነስተኛ መስኖ ግድቦች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑን የዞኑ መስኖ ልማት ጽሕፈት ቤት አስታወቀ።


የኢሉ አባቦር ዞን መስኖ ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ደመቁ ተረፈ እንዳሉት፥ አነስተኛ መስኖ ግድቦች ግንባታው በሁለት ወረዳዎች እየተከናወነ ነው።


የክልሉ መንግስት 'ፊና' በተሰኘ ፕሮጀክት ውኃ አጠር በሆኑ አካባቢዎች አነስተኛና መለስተኛ የመስኖ ግድቦች ግንባታ እያካሄደ ሲሆን በዞኑ በግንባታ ላይ የሚገኙ ግድቦችም የዚሁ አካል ናቸው ብለዋል።


የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ሲጠናቀቅ የአካባቢው አርሶ አደሮችን የማምረት አቅም በማሳደግ ተጠቃሚ የሚያደርጋቸው እንደሆነ ገልጸዋል።


በሁለቱ ወረዳዎች 4 ሺህ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ማድረግ የሚችሉት እነዚሁ ግድቦች ግንባታቸው በ400 ሚሊዮን ብር ወጪ ነው እየተከናወነ የሚገኘው ብለዋል።


ግድቦቹ በሚገነቡበት አካባቢ የሚኖሩ አርሶ አደሮችም የመስኖ ግድቦቹ ከክረምት ባለፈ በበጋ ወራት ተጨማሪ የማምረት አቅም እንደሚፈጥርላቸው ተናግረዋል።


አርሶ አደር አበበ ሀብተወልድ ፕሮጀክቶቹ በአካባቢያቸው የሚገኘውን ወንዝ በግብርና ስራቸው ላይ በመጠቀም ክረምትና በጋ ማምረት የሚያስችለን ነው ብለዋል።


በዚህም ፕሮጀክቱ ተጠናቆ ወደስራ ሲገባ በዝናብ ወቅት ብቻ ላይ የተመሰረተውን ግብርናቸውን በማሻሻል ዓመቱን ሙሉ ማምረት እንደሚያስችላቸው ገልጸዋል።


ሌላው አቶ ጫንያለው ያደታ ደግሞ የመስኖ ግድቡ በግብርና ስራ እያከናወኗቸው ባሉ የተለያዩ ኢኒሼቲቮች ላይ ያላቸው ተሳትፎ እንዲጨምር ይረዳል ብለዋል።


በአካባቢያቸው ሌሎች የግብርና ስራዎችም ላይ ጠንክረው በመስራት ሁለንተናዊ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ እንደሚያግዛቸው አክለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026