የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

የኢትዮጵያ ታምርት የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ዓላማ የኢትዮጵያን ምርት ለዓለም ማስተዋወቅ ነው - ሚኒስትር መላኩ አለበል

Apr 27, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ዓላማ የኢትዮጵያን ምርት ለዓለም ማስተዋወቅ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።

የ2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር በመስቀል አደባባይ እየተካሄደ ነው።

ውድድሩን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን፥ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 4ኛ ዓመትን አስመልክቶ የተሰናዳ መሆኑ ተገልጿል።


የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በውድድሩ ማስጀመሪያ ላይ እንደገለጹት፥ የጎዳና ላይ ውድድሩ ዓላማ የኢትዮጵያን ምርት ለዓለም ማስተዋወቅ ነው።

አምራችና ጤናማ ትውልድ ለማፍራት ስፖርታዊ ውድድሩ ትልቅ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል።

በውድድሩ የውጭ ሀገራት አምባሳደሮች፣ ክለቦችና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በዓለም አደባባይ በሚደምቅበት የአትሌቲክስ ስፖርት ውድድር መካሄዱ የኢንዱስትሪ ምርቶችን ለማስተዋወቅ ገንቢ ሚና እንዳለውም አንስተዋል።

መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ላደረገው የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር መካሄድ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ድርጅቶች፣ ግለሰቦችና ተወዳዳሪዎች ምስጋና አቅርበዋል።


የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፥ ያለፉት የለውጥ ዓመታት የስፖርት ልማት ስራዎች ስፖርት ህዝባዊ መሰረት እንዲኖረው እያስቻሉ ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ ከውጪ ይገቡ የነበሩ የስፖርት ትጥቅ አልባሳትን በሀገር ውስጥ በጥራት በማምረት ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በሩጫ ውድድሩ በሁለቱም ፆታዎች በቅደም ተከተል ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች የ300ሺህ፣ የ200ሺህ እና የ100ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት የሚበረከትላቸው ይሆናል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በ2014 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የኢትዮጵያ ታምርት ሀገራዊ ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪ ማነቆዎችን በዘላቂነት በመፍታት መዋቅራዊ ሽግግር፣ ተወዳዳሪ፣ ምቹ የቢዝነስ ከባቢያዊ ሁኔታን የመፍጠር እንዲሁም በሀገር ውስጥ ትላልቅ አምራች ኢንዱስትሪዎችን የመገንባት ዓላማን ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025