
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 19/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር ዓላማ የኢትዮጵያን ምርት ለዓለም ማስተዋወቅ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።
የ2017 ዓ.ም ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ የ10 ኪሎ ሜትር የጎዳና ላይ የሩጫ ውድድር በመስቀል አደባባይ እየተካሄደ ነው።
ውድድሩን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን፥ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ 4ኛ ዓመትን አስመልክቶ የተሰናዳ መሆኑ ተገልጿል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በውድድሩ ማስጀመሪያ ላይ እንደገለጹት፥ የጎዳና ላይ ውድድሩ ዓላማ የኢትዮጵያን ምርት ለዓለም ማስተዋወቅ ነው።
አምራችና ጤናማ ትውልድ ለማፍራት ስፖርታዊ ውድድሩ ትልቅ ሚና እንዳለውም ተናግረዋል።
በውድድሩ የውጭ ሀገራት አምባሳደሮች፣ ክለቦችና የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ እንደሚገኙ አስታውቀዋል።
የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ በዓለም አደባባይ በሚደምቅበት የአትሌቲክስ ስፖርት ውድድር መካሄዱ የኢንዱስትሪ ምርቶችን ለማስተዋወቅ ገንቢ ሚና እንዳለውም አንስተዋል።
መነሻና መድረሻውን መስቀል አደባባይ ላደረገው የ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር መካሄድ አስተዋጽኦ ላበረከቱ ድርጅቶች፣ ግለሰቦችና ተወዳዳሪዎች ምስጋና አቅርበዋል።

የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ሸዊት ሻንካ፥ ያለፉት የለውጥ ዓመታት የስፖርት ልማት ስራዎች ስፖርት ህዝባዊ መሰረት እንዲኖረው እያስቻሉ ነው ብለዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ ከውጪ ይገቡ የነበሩ የስፖርት ትጥቅ አልባሳትን በሀገር ውስጥ በጥራት በማምረት ጥቅም ላይ እንዲውሉ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።
በሩጫ ውድድሩ በሁለቱም ፆታዎች በቅደም ተከተል ከ1ኛ እስከ 3ኛ ደረጃ ለሚወጡ ተወዳዳሪዎች የ300ሺህ፣ የ200ሺህ እና የ100ሺህ ብር የገንዘብ ሽልማት የሚበረከትላቸው ይሆናል።
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በ2014 ዓ.ም ይፋ የተደረገው የኢትዮጵያ ታምርት ሀገራዊ ንቅናቄ የአምራች ኢንዱስትሪ ማነቆዎችን በዘላቂነት በመፍታት መዋቅራዊ ሽግግር፣ ተወዳዳሪ፣ ምቹ የቢዝነስ ከባቢያዊ ሁኔታን የመፍጠር እንዲሁም በሀገር ውስጥ ትላልቅ አምራች ኢንዱስትሪዎችን የመገንባት ዓላማን ታሳቢ ያደረገ መሆኑ ይታወቃል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026