የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የግብርና ሥራን የሚያዘምኑ አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶች ላይ ትኩረት አድርገናል-በፈጠራ ሥራ የተሰማሩ ወጣቶች

May 6, 2025

IDOPRESS

ደሴ፤ ሚያዚያ 23/2017(ኢዜአ)፡-የግብርና ሥራን ጊዜና ወጪ መቆጠብ የሚያስችሉ አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶች ላይ ትኩረት ማድረጋቸውን በፈጠራ ሥራ የተሰማሩ ወጣቶች ገለጹ።

በኮምቦልቻ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የአማራ ክልል 9ኛው የቴክኖሎጂ፣ የክህሎት፣ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር እንዲሁም የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የንግድ ትርዒት እና የደረጃ ሽግግር ሳምንት ዛሬ ተጠናቋል።

የቴክኖሎጂ መዘመንና የዲጂታላይዜሽን መስፋፋትን ተከትሎ በየአካባቢው ያሉ ወጣቶች ከጊዜው ጋር የሚራመዱ የፈጠራ ውጤቶችን በማበርከት ላይ ይገኛሉ።

በተለይም የኢትዮጵያን የግብርና ሥራ በማዘመን እና ጊዜንና ወጪን በመቀነስ ምርታማነትን የሚጨምሩ ቴክኖሎጂዎችን ማስፋፋት ላይ በርካታ ወጣቶች እየሰሩ ናቸው።

በ ንግድ ትርዒት እና የደረጃ ሽግግር ሳምንት ከተሳተፉ ወጣቶች መካከል የጎንደር ከተማ ነዋሪው ወጣት ውብሸት ታዬ የእንሰሳት መኖ ማቀነባበሪያ እና የበቆሎ መፈልፈያ ማሽን መስራቱን ይገልጻል።

የወጣቱ የፈጠራ ሥራ የእንስሳት መኖን በቀላሉ በማቀነባበር እንዲሁም በቆሎን በፍጥነት በመፈልፈል የአርሶ አደሩን ጉልበትና ጊዜ እንደሚቆጥብ ተናግሯል።

የበቆሎ መፈልፈያ ማሽኑ ጊዜን መቆጠብ የሚችልና ተረፈ ምርቱን በመጠቀም ለእንስሳት መኖ በቀላሉ የሚያቀነባብር መሆኑንም ይናገራል።


ሌላው ተሳታፊ የከሚሴ ከተማ ነዋሪው ወጣት ሰይድ አህመድ ደግሞ፤ በቀን ሁለት ሄክታር መሬት ማረስ የሚችል ማሽን በመፍጠር ይፋ አድርጓል።

እንደ ወጣቱ ገለጻ በአንድ ሰው ብቻ የሚንቀሳቀሰው ይህ ማሽን ከእርሻ ሥራ ባለፈ የውሃ መሳቢያ ሞተር ጭምር የተገጠመለት በመሆኑ ለግብርና ሥራ ጠቀሜታው የላቀ ነው።


በመሆኑም የፈጠራ ሥራውን በቴክኖሎጂ በማስደገፍና በማስፋት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ የማድረግ ዕቅድ እንዳለው ጠቅሶ፣ ለስኬቱ ድጋፍ ያስፈልጋል ብሏል።

በወሎ ዩኒቨርሲቲ የኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የምህንድስና ትምህርት ክፍል መምህር ኢንጂነር አብዱልከሪም ሰይድ፤ የወጣቶቹ የፈጠራ ውጤት በተለይ ለግብርና ዘርፍ ትልቅ ተስፋ መሆኑን ተናግረዋል።

የፈጠራ ሥራዎቹ ይበልጥ ዳብረውና በብዛት ተመርተው ለአርሶ አደሮች ተደራሽ እንዲሆኑም የሁሉም ድጋፍና ትብብር ያስፈልጋል ብለዋል።


የአማራ ክልል ሥራና ስልጠና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አወቀ ዘመነ በበኩላቸው፤ የወጣቹን የፈጠራ ሥራዎች አድንቀው በስፋት ጥቅም ላይ እንዲውሉ የማገዝና የማበረታታት ሥራ ይሰራል ብለዋል።

በክልሉ 121 የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎችን በማወዳደር የተሻሉት ተለይተው በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲወዳደሩ የሚደረግ መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026