
ደሴ፤ ሚያዚያ 23/2017(ኢዜአ)፡-የግብርና ሥራን ጊዜና ወጪ መቆጠብ የሚያስችሉ አዳዲስ የፈጠራ ውጤቶች ላይ ትኩረት ማድረጋቸውን በፈጠራ ሥራ የተሰማሩ ወጣቶች ገለጹ።
በኮምቦልቻ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የአማራ ክልል 9ኛው የቴክኖሎጂ፣ የክህሎት፣ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር እንዲሁም የጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የንግድ ትርዒት እና የደረጃ ሽግግር ሳምንት ዛሬ ተጠናቋል።
የቴክኖሎጂ መዘመንና የዲጂታላይዜሽን መስፋፋትን ተከትሎ በየአካባቢው ያሉ ወጣቶች ከጊዜው ጋር የሚራመዱ የፈጠራ ውጤቶችን በማበርከት ላይ ይገኛሉ።
በተለይም የኢትዮጵያን የግብርና ሥራ በማዘመን እና ጊዜንና ወጪን በመቀነስ ምርታማነትን የሚጨምሩ ቴክኖሎጂዎችን ማስፋፋት ላይ በርካታ ወጣቶች እየሰሩ ናቸው።
በ ንግድ ትርዒት እና የደረጃ ሽግግር ሳምንት ከተሳተፉ ወጣቶች መካከል የጎንደር ከተማ ነዋሪው ወጣት ውብሸት ታዬ የእንሰሳት መኖ ማቀነባበሪያ እና የበቆሎ መፈልፈያ ማሽን መስራቱን ይገልጻል።
የወጣቱ የፈጠራ ሥራ የእንስሳት መኖን በቀላሉ በማቀነባበር እንዲሁም በቆሎን በፍጥነት በመፈልፈል የአርሶ አደሩን ጉልበትና ጊዜ እንደሚቆጥብ ተናግሯል።
የበቆሎ መፈልፈያ ማሽኑ ጊዜን መቆጠብ የሚችልና ተረፈ ምርቱን በመጠቀም ለእንስሳት መኖ በቀላሉ የሚያቀነባብር መሆኑንም ይናገራል።

ሌላው ተሳታፊ የከሚሴ ከተማ ነዋሪው ወጣት ሰይድ አህመድ ደግሞ፤ በቀን ሁለት ሄክታር መሬት ማረስ የሚችል ማሽን በመፍጠር ይፋ አድርጓል።
እንደ ወጣቱ ገለጻ በአንድ ሰው ብቻ የሚንቀሳቀሰው ይህ ማሽን ከእርሻ ሥራ ባለፈ የውሃ መሳቢያ ሞተር ጭምር የተገጠመለት በመሆኑ ለግብርና ሥራ ጠቀሜታው የላቀ ነው።

በመሆኑም የፈጠራ ሥራውን በቴክኖሎጂ በማስደገፍና በማስፋት ለአርሶ አደሩ ተደራሽ የማድረግ ዕቅድ እንዳለው ጠቅሶ፣ ለስኬቱ ድጋፍ ያስፈልጋል ብሏል።
በወሎ ዩኒቨርሲቲ የኮምቦልቻ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የምህንድስና ትምህርት ክፍል መምህር ኢንጂነር አብዱልከሪም ሰይድ፤ የወጣቶቹ የፈጠራ ውጤት በተለይ ለግብርና ዘርፍ ትልቅ ተስፋ መሆኑን ተናግረዋል።
የፈጠራ ሥራዎቹ ይበልጥ ዳብረውና በብዛት ተመርተው ለአርሶ አደሮች ተደራሽ እንዲሆኑም የሁሉም ድጋፍና ትብብር ያስፈልጋል ብለዋል።

የአማራ ክልል ሥራና ስልጠና ቢሮ ምክትል ኃላፊ አወቀ ዘመነ በበኩላቸው፤ የወጣቹን የፈጠራ ሥራዎች አድንቀው በስፋት ጥቅም ላይ እንዲውሉ የማገዝና የማበረታታት ሥራ ይሰራል ብለዋል።
በክልሉ 121 የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎችን በማወዳደር የተሻሉት ተለይተው በሀገር አቀፍ ደረጃ እንዲወዳደሩ የሚደረግ መሆኑንም ገልጸዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026