የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የቴክኖሎጂና የፈጠራ ውድድሩ የተሻለ በማምረት ተጠቃሚነትን ማሳደግ የሚያስችል ልምድና ትስስር ፈጥሮልናል - ተሳታፊዎች

May 6, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፤ ሚያዝያ 24/2017(ኢዜአ)፦ በውድድሩ የተሻለ በማምረት ተጠቃሚነትን ማሳደግ የሚያስችል ልምድና የገበያ ትስስር ማግኘታቸውን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል የቴክኖሎጂና የፈጠራ ውድድር ተሳታፊዎች ገለጹ።

በክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ''ብሩህ አዕምሮዎች፣ በክህሎት የበቁ ዜጎች'' በሚል መሪ ሐሳብ የክህሎት፣ የቴክኖሎጂና የተግባራዊ ጥናትና ምርምር ውድድርና ዐውደ ርዕይ በቦንጋ ከተማ ተካሂዷል።


በቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአግሮ ፕሮሰሲንግ መምህር ሙሉቀን መኮንን፣ በኮሌጁ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን እየሰሩ እንዳሉ ገልጸዋል።

ውድድሩ ለቴክኖሎጂ ፈጣሪዎች ልዩ ትርጉም እንዳለው ጠቅሰው፣ በበለጠ ለማምረትና ተጠቃሚ መሆን የሚያስችል ልምድና የገበያ ትስስር የተፈጠሩበት መሆኑን ተናግረዋል።

ለውድድሩ ከወዳደቁ ቁሶች የተሰራ የፈሳሽ ሳሙና ማምረቻ ማሽን ይዘው መቅረባቸውን ጠቁመው፣ ምርቱን በዝቅተኛ ዋጋ በማቅረብ ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ማሽን ይዘው ለውድድር የቀረቡት የቴፒ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መምህር በልስቲ ይታየው፣ ውድድሩ የፈጠራ ሥራቸውን አሻሽለው ለመስራት ልምድና ሀሳብ ያገኙበት መሆኑን ተናግረዋል።

በውድድሩ ይዘው የቀረቡት የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽን ጊዜና ጉልበት ስለሚቆጥብ በእንስሳት አርባታና ማድለብ ሥራ የተሰማሩ ማህበራትና ግለሰቦችን ተጠቃሚ ያደርጋል ብለዋል።


የቦንጋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኤሌክትሮ ቴክኖሎጂ የትምህርት ክፍል ሰልጣኝ አዲሱ አቢ፣ በኮሌጁ በተሰጠው ተግባር ተኮር ስልጠና ታግዞ የተለያዩ የፈጠራ ሥራዎችን እየሰራ መሆኑን ተናግሯል።

ከእነዚህ መካከል የትራፊክ እንቅስቃሴ ቁጥጥር ስራን የሚያግዝና የሚያዘምን የትራፊክ መብራት በውድድር ላይ ይዞ መቅረቡን ገልጾ፣ በውድድሩ ለቀጣይ ስራው የሚሆን ጠቃሚ ግብዓቶች ማግኘቱን ገልጿል።


የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ምክትልና የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ኃላፊ ቤተልሔም ዳንኤል በበኩላቸው፣ በክልሉ የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ኮሌጆች ቴክኖሎጂን የሚፈጥሩና የሚቀዱ ዜጎችን ለማፍራት በትኩረት እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።

የስልጠና አሰጣጡ የክልሉን ጸጋዎች መሰረት ያደረገና የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱ ቴክኖሎጂዎች ላይ ማተኮሩን ጠቁመው በውድድሩ የቀረቡ የፈጠራ ውጤቶችም ይህንን በተጨባጭ ያሳዩ ናቸው ብለዋል።

እንደ ኃላፊዋ ገለጻ በውድድሩ ሦስት የጥናትና ምርምር፣ 14 የቴክኖሎጂ እንዲሁም 24 የክህሎት ሥራዎች ቀርበዋል።


የክልሉ ሥራና ክህሎት ቢሮ ሃላፊ አብይ አንደሞ(ዶ/ር) በሰጡት አስተያየት በክልሉ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንዲፈጥሩና የፈጠሩትን አጠናክረው እንዲሄዱ ትኩረት ተደርጓል።

ተቋማቱ የህብረተሰቡን ችግር የሚፈቱና የመግዛት አቅምን ያገናዘቡ የተለያዩ ቴክኖሎጂዎችን በጥራት እያመረቱ መሆናቸውን ጠቁመው፣ የፈጠራ ውጤቶቹን ወደ ህብረተሰቡ የማሰራጨት ሥራ ይሰራል ብለዋል።

ለሁለት ተከታታይ ቀናት በተካሄደ ውድድር ላይ በአሰልጣኝ መምህራንና ሰልጣኞች የተሰሩ የተለያዩ የቴክኖሎጂ፣ የፈጠራ እና የምርምር ሥራዎች ለውድድር የቀረቡ ሲሆን አሸናፊ ለሆኑት ማበረታቻ ሽልማትና ዕውቅና ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026