የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በሐረሪ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ መሻሻል ታይቷል - ተገልጋዮች

May 6, 2025

IDOPRESS

ሐረር ፤ሚያዝያ 27/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ መሻሻል መታየቱን ተገልጋዮች ተናገሩ።

በቢሮው የተገኘው የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ሪፖርተር ያነጋገራቸው ተገልጋዮች እንዳሉት ቀደም ሲል ቢሮው ከመሬትና መሬት ነክ ከሆኑ ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የባለ ጉዳይ መጉላላት ይታይ እንደነበር አስታውሰዋል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የነበረው እንግልት በመቃለሉ መሻሻል ማሳየቱን ገልጸው፤ ይህም ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

ከተገልጋዮች መካከል አቶ አማረ አለማየሁ በቅርቡ ከልማት ጋር በተያያዘ መኖሪያ ቤታቸው መፍረሱን ገልጸው፤ አሁን ግን አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ምትክ መሬት እንደተሰጣቸው አስረድተዋል።

ቢሮው ቀደም ሲል የነበሩበትን የአሰራር ችግሮች በመቅረፍ ለተገልጋዩ ማህበረሰብ እየሰጠ የሚገኘው ተግባር አበረታችና በቀጣይም ሊጠናከር እንደሚገባም አስተያየት ሰጥተዋል።

ቀደም ሲል ጉዳዮችን ለማስፈፀም ወደ ተቋሙ በሚመጡበት ወቅት መጉላላትና ምልልስ ይበዛው እንደነበር ያስታወሱት ደግሞ ወይዘሮ ፍሪ ሞገስ ናቸው።

በአሁኑ ወቅት ግን ይታዩ የነበሩ ችግሮች መቀረፋቸውን ገልጸው፤ በተለይ የተቋሙ የተለያዩ የስራ ክፍል ሃላፊዎች በሰዓቱ ወደ ቢሯቸው እንደሚገቡና ተገልጋዩንም በአግባቡ እንደሚያስተናግዱ ገልጸዋል።

መምህርት እሌኒ እሸቱ በበኩላቸው ቀደም ሲል በተቋሙ የስራ ሰዓትን አክብሮ ለተገልጋዩ ቀልጣፋ አገልግሎት የመስጠት ሁኔታ ውስንነት ይታይበት እንደነበር ገልጸው፤ አሁን ግን የስራ ሰዓትን አክብሮ ከመገኘት አንጻር መሻሻሎች ታይተዋል ብለዋል።

ለአንድ ጉዳይ የነበረው መመላለስም እየተቀረፈ እንደሚገኝ የጠቆሙት መምህርት እሌኒ ይህም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የሐረሪ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሃላፊ አቶ ሙክታር ሳሊህ እንደሚሉት በቢሮው ቀደም ሲል ከመልካም አስተዳደርና ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ ውስንነቶች ነበሩ።

በዚህም የሪፎርም ስራዎችን በማከናወን በቢሮ ውስጥ የሚስተዋሉና ለተገልጋዩ እንቅፋት የሆኑ ውስንነቶችን የመቅረፍ ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል።

በቢሮው የተጀመሩ ቀልጣፋ የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደትን ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ አሰራሮችን በቴክኖሎጂ የማዘመን ስራ እየተከናወነ መሆኑንም ተናግረዋል።

ይህም ከአገልግሎት አሰጣጥ፣ ከፋይል መሰወር፣ ከብልሹ አሰራሮችና ሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የሚስተዋለውን ክፍተት እንደሚያቃልልም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025