የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

May 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 27/2017(ኢዜአ)፦አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ ገለጹ።

ሶስተኛ ቀኑን ያስቆጠረው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን ማብቃት ማሳደግና ተወዳዳሪነት ሽግግር ማፋጠን በሚል ርእሰ ጉዳይ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።


በመድረኩ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ኢንስቲትዩት፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ፖሊሲና እና ስትራተጂ በመቅረጽ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ እየተሰራ ይገኛል።

በተለይም ከአቅም ግንባታ አኳያ በርካታ ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።


የኢንዱስትሪዎችን ማነቆ የሆነውን የመስሪያና መሸጫ ቦታዎች ችግር ለመቅረፍ በተደረገው ጥረትም መሻሻል መታየቱ አንስተዋል።

እንዲሁም የፋይናንስ አቅርቦት ችግራቸውንም ለመቅረፍ ከባንኮች ጋር ትስስር በመፍጠር ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በተደረገላቸው ድጋፍም የሚያመርቷቸው ምርቶች ጥራት እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025