የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ ነው

May 6, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 27/2017(ኢዜአ)፦አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ ገለጹ።

ሶስተኛ ቀኑን ያስቆጠረው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን ማብቃት ማሳደግና ተወዳዳሪነት ሽግግር ማፋጠን በሚል ርእሰ ጉዳይ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።


በመድረኩ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ኢንስቲትዩት፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ፖሊሲና እና ስትራተጂ በመቅረጽ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ እየተሰራ ይገኛል።

በተለይም ከአቅም ግንባታ አኳያ በርካታ ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።


የኢንዱስትሪዎችን ማነቆ የሆነውን የመስሪያና መሸጫ ቦታዎች ችግር ለመቅረፍ በተደረገው ጥረትም መሻሻል መታየቱ አንስተዋል።

እንዲሁም የፋይናንስ አቅርቦት ችግራቸውንም ለመቅረፍ ከባንኮች ጋር ትስስር በመፍጠር ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

በተደረገላቸው ድጋፍም የሚያመርቷቸው ምርቶች ጥራት እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026