
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 27/2017(ኢዜአ)፦አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችሉ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ ገለጹ።
ሶስተኛ ቀኑን ያስቆጠረው ኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ አነስተኛ እና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞችን ማብቃት ማሳደግና ተወዳዳሪነት ሽግግር ማፋጠን በሚል ርእሰ ጉዳይ ውይይት እየተካሄደ ይገኛል።

በመድረኩ ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ኢንስቲትዩት፣ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
የኢንዱስትሪ ሚኒስትር ዴኤታ ታረቀኝ ቡሉልታ በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ፖሊሲና እና ስትራተጂ በመቅረጽ ይበልጥ ውጤታማ እንዲሆኑ እየተሰራ ይገኛል።
በተለይም ከአቅም ግንባታ አኳያ በርካታ ውጤታማ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል።

የኢንዱስትሪዎችን ማነቆ የሆነውን የመስሪያና መሸጫ ቦታዎች ችግር ለመቅረፍ በተደረገው ጥረትም መሻሻል መታየቱ አንስተዋል።
እንዲሁም የፋይናንስ አቅርቦት ችግራቸውንም ለመቅረፍ ከባንኮች ጋር ትስስር በመፍጠር ለመቅረፍ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
በተደረገላቸው ድጋፍም የሚያመርቷቸው ምርቶች ጥራት እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026