የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በማምረት ላይ የተመሰረተ ኢኮኖሚ የመገንባት ፍላጎትን ማሳካት ያስችላል - ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ

May 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በማምረት ላይ የተመሰረተ ኢኮኖሚ የመገንባት ፍላጎትን ማሳካት የሚያስችል መደላድል የሚፈጥር መሆኑን ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ፡፡

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ያለውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2017 ጎብኝተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከሚያዚያ 25 እስከ 29 ቀን 2017 ዓ.ም የሚቆየውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2017 በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኢንዱስትሪዎች የሚያጋጥማቸውን ችግሮች በመፍታት የማምረት አቅማቸው አጎልብቷል፤ በኤክስፖውም ከ288 በላይ አምራቾች እየተሳተፉበት ነው፡፡


ፕሬዚዳንት ታዬ ከጉብኝቱ በኋላ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ መንገድ ማምረትና ምርታማነትን በመጨመር ጥቅል ሀገራዊ እድገትን ማሳደግ ነው።

የአንድ ሀገር እድገት የሚመሰረተው በማምረት መሆኑን ገልጸው፤ በማምረት ላይ የተሰማሩ ሀገራት ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እድገት እንደሚያሳዩ ተናግረዋል፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪውን የማምረት አቅም በማሳደግ የሥራ እድል የሚፈጥርና ነገ የተሻለ ለማምረት መሰረት የሚጥል መሆኑን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በማምረት ላይ የተመሰረተ ኢኮኖሚ ለመገንባት የምናስበውን እውን ማድረግ የሚያስችል መደላድል ይፈጥራል ብለዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያዘጋጀው የኢትዮጵያ ታምርት መርሐ ግብር ዘርፉን በማነቃቃት በዜጎች ዘንድ የእንችላለን መንፈስን ያላበሰ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ኤክስፖው ኢትዮጵያ የማምረት አቅም እንዳላት የሚያሳይ ነው፤ በተስፋ እንድንናፍቅ የሚያደርጉ ምርቶች የቀረቡበት ነው ብለዋል፡፡

በኤክስፖው ከቆዳ የተሰሩ የተለያዩ ምርቶች በዓለም አቀፍ የጥራት መመዘኛ መስፈርት ደረጃቸውን ያሟሉ መሆናቸውን ተመልክቻለሁ ብለዋል።


በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶች የቀረቡበት መሆኑን ገልጸው፤ ምርቶቹን የኢትዮጵያን መቻል የሚገልጡ፤ የሰዎችን ብልህነት የሚያሳዩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ በራስ ምርት የመኩራት ባህል ዝቅተኛ መሆኑን ገልጸው፤ ይህንን የተሳሳተ ምልከታ ማስወገድ ይገባል ብለዋል፡፡

የዓለም ገበያ ሰፊ፣ ሸማቹ በርካታ መሆኑን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ መሰረታዊው ጉዳይ የምርት ጥራት መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርቶች ብዙ የሚያስኬዱ ለእኛ ዓይን ከፋች፣ በዓለም ገበያ መስፋፋት የሚችሉ መሆናቸውምን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026