
አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በማምረት ላይ የተመሰረተ ኢኮኖሚ የመገንባት ፍላጎትን ማሳካት የሚያስችል መደላድል የሚፈጥር መሆኑን ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ፡፡
የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ያለውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2017 ጎብኝተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከሚያዚያ 25 እስከ 29 ቀን 2017 ዓ.ም የሚቆየውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2017 በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኢንዱስትሪዎች የሚያጋጥማቸውን ችግሮች በመፍታት የማምረት አቅማቸው አጎልብቷል፤ በኤክስፖውም ከ288 በላይ አምራቾች እየተሳተፉበት ነው፡፡

ፕሬዚዳንት ታዬ ከጉብኝቱ በኋላ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ መንገድ ማምረትና ምርታማነትን በመጨመር ጥቅል ሀገራዊ እድገትን ማሳደግ ነው።
የአንድ ሀገር እድገት የሚመሰረተው በማምረት መሆኑን ገልጸው፤ በማምረት ላይ የተሰማሩ ሀገራት ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እድገት እንደሚያሳዩ ተናግረዋል፡፡
የአምራች ኢንዱስትሪውን የማምረት አቅም በማሳደግ የሥራ እድል የሚፈጥርና ነገ የተሻለ ለማምረት መሰረት የሚጥል መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በማምረት ላይ የተመሰረተ ኢኮኖሚ ለመገንባት የምናስበውን እውን ማድረግ የሚያስችል መደላድል ይፈጥራል ብለዋል፡፡
የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያዘጋጀው የኢትዮጵያ ታምርት መርሐ ግብር ዘርፉን በማነቃቃት በዜጎች ዘንድ የእንችላለን መንፈስን ያላበሰ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ኤክስፖው ኢትዮጵያ የማምረት አቅም እንዳላት የሚያሳይ ነው፤ በተስፋ እንድንናፍቅ የሚያደርጉ ምርቶች የቀረቡበት ነው ብለዋል፡፡
በኤክስፖው ከቆዳ የተሰሩ የተለያዩ ምርቶች በዓለም አቀፍ የጥራት መመዘኛ መስፈርት ደረጃቸውን ያሟሉ መሆናቸውን ተመልክቻለሁ ብለዋል።

በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶች የቀረቡበት መሆኑን ገልጸው፤ ምርቶቹን የኢትዮጵያን መቻል የሚገልጡ፤ የሰዎችን ብልህነት የሚያሳዩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡
በኢትዮጵያ በራስ ምርት የመኩራት ባህል ዝቅተኛ መሆኑን ገልጸው፤ ይህንን የተሳሳተ ምልከታ ማስወገድ ይገባል ብለዋል፡፡
የዓለም ገበያ ሰፊ፣ ሸማቹ በርካታ መሆኑን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ መሰረታዊው ጉዳይ የምርት ጥራት መሆኑን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርቶች ብዙ የሚያስኬዱ ለእኛ ዓይን ከፋች፣ በዓለም ገበያ መስፋፋት የሚችሉ መሆናቸውምን ገልጸዋል፡፡
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026