የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በማምረት ላይ የተመሰረተ ኢኮኖሚ የመገንባት ፍላጎትን ማሳካት ያስችላል - ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ

May 7, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ሚያዝያ 28/2017(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በማምረት ላይ የተመሰረተ ኢኮኖሚ የመገንባት ፍላጎትን ማሳካት የሚያስችል መደላድል የሚፈጥር መሆኑን ፕሬዚዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ ገለጹ፡፡

የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል እየተካሄደ ያለውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2017 ጎብኝተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከሚያዚያ 25 እስከ 29 ቀን 2017 ዓ.ም የሚቆየውን የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ 2017 በይፋ ማስጀመራቸው ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ኢንዱስትሪዎች የሚያጋጥማቸውን ችግሮች በመፍታት የማምረት አቅማቸው አጎልብቷል፤ በኤክስፖውም ከ288 በላይ አምራቾች እየተሳተፉበት ነው፡፡


ፕሬዚዳንት ታዬ ከጉብኝቱ በኋላ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ መንገድ ማምረትና ምርታማነትን በመጨመር ጥቅል ሀገራዊ እድገትን ማሳደግ ነው።

የአንድ ሀገር እድገት የሚመሰረተው በማምረት መሆኑን ገልጸው፤ በማምረት ላይ የተሰማሩ ሀገራት ከፍተኛ ኢኮኖሚያዊ እድገት እንደሚያሳዩ ተናግረዋል፡፡

የአምራች ኢንዱስትሪውን የማምረት አቅም በማሳደግ የሥራ እድል የሚፈጥርና ነገ የተሻለ ለማምረት መሰረት የሚጥል መሆኑን ገልጸዋል።


የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በማምረት ላይ የተመሰረተ ኢኮኖሚ ለመገንባት የምናስበውን እውን ማድረግ የሚያስችል መደላድል ይፈጥራል ብለዋል፡፡

የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ያዘጋጀው የኢትዮጵያ ታምርት መርሐ ግብር ዘርፉን በማነቃቃት በዜጎች ዘንድ የእንችላለን መንፈስን ያላበሰ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ኤክስፖው ኢትዮጵያ የማምረት አቅም እንዳላት የሚያሳይ ነው፤ በተስፋ እንድንናፍቅ የሚያደርጉ ምርቶች የቀረቡበት ነው ብለዋል፡፡

በኤክስፖው ከቆዳ የተሰሩ የተለያዩ ምርቶች በዓለም አቀፍ የጥራት መመዘኛ መስፈርት ደረጃቸውን ያሟሉ መሆናቸውን ተመልክቻለሁ ብለዋል።


በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ምርቶች የቀረቡበት መሆኑን ገልጸው፤ ምርቶቹን የኢትዮጵያን መቻል የሚገልጡ፤ የሰዎችን ብልህነት የሚያሳዩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

በኢትዮጵያ በራስ ምርት የመኩራት ባህል ዝቅተኛ መሆኑን ገልጸው፤ ይህንን የተሳሳተ ምልከታ ማስወገድ ይገባል ብለዋል፡፡

የዓለም ገበያ ሰፊ፣ ሸማቹ በርካታ መሆኑን የገለጹት ፕሬዝዳንቱ፤ መሰረታዊው ጉዳይ የምርት ጥራት መሆኑን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ምርቶች ብዙ የሚያስኬዱ ለእኛ ዓይን ከፋች፣ በዓለም ገበያ መስፋፋት የሚችሉ መሆናቸውምን ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026