የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በከተማው የዲጂታላይዜሽን አሰራርን በመተግበር የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት በትኩረት እየተሰራ ነው

May 8, 2025

IDOPRESS

ባህር ዳር፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ዲጂታላይዜሽን አሰራርን በመተግበር ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ።

ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው እንደገለጹት አስተዳደሩ የዲጂታላይዜሽን አሰራርን በመተግበርና ፈጣን አገልግሎት በመስጠት የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።

በዚህም የቦታ፣ የቤት፣ የመኪናና ሌሎች ንብረቶችን የያዙ 100ሺህ ፋይሎችን ወደ ኮምፒውተር በማስገባት ዘመኑን የሚመጥን የመረጃ አያያዝ ስርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ይህም ከተማዋን ስማርት ሲቲ ከማድረግ ጋር ተያይዞ አሰራሮችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ለህብረተሰቡ ከብልሹ አሰራር የጸዳና ፈጣን አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።

በቴክኖሎጂ የተደገፈው አሰራር ተገልጋዮች የተለያዩ ሰነዶችን በሚጠይቁበት ወቅት የሚገጥማቸውን እንግልት እንደሚያስቀር ገልጸዋል።

ፋይሎችን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር እስከ ግንቦት ወር መጨረሻ በማጠናቀቅ ለዜጎች ፍትሃዊና ቀልጠፋ አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

አሁን ላይ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የመሬት ማኔጅመንት(ካዳስተር) ስራ ከፍተኛ በጀት ተመድቦ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው በዚህም ስለከተማዋ መሬት የተሟላ መረጃ ማግኘት የሚቻልበት ሁኔታ ይፈጠራል ብለዋል።

በተጨማሪም የተቋም ግንባታ ላይ በማተኮር ከተማዋን ለቱሪዝም፣ ለኢንቨስትመንትና ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎች እየተከናወኑ እንደሆነም ገልፀዋል።

የባህር ዳር ከተማን ስማርት ሲቲ ማድረግን ታሳቢ ያደረጉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት በየዘርፉ እየተከናወኑ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025