
ባህር ዳር፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ በባህር ዳር ከተማ አስተዳደር ዲጂታላይዜሽን አሰራርን በመተግበር ለህብረተሰቡ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት እየተሰራ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ ጎሹ እንዳላማው ገለጹ።
ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባው እንደገለጹት አስተዳደሩ የዲጂታላይዜሽን አሰራርን በመተግበርና ፈጣን አገልግሎት በመስጠት የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ ነው።
በዚህም የቦታ፣ የቤት፣ የመኪናና ሌሎች ንብረቶችን የያዙ 100ሺህ ፋይሎችን ወደ ኮምፒውተር በማስገባት ዘመኑን የሚመጥን የመረጃ አያያዝ ስርዓት ለመዘርጋት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
ይህም ከተማዋን ስማርት ሲቲ ከማድረግ ጋር ተያይዞ አሰራሮችን ዲጂታላይዝ በማድረግ ለህብረተሰቡ ከብልሹ አሰራር የጸዳና ፈጣን አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ ያለመ መሆኑን አስረድተዋል።
በቴክኖሎጂ የተደገፈው አሰራር ተገልጋዮች የተለያዩ ሰነዶችን በሚጠይቁበት ወቅት የሚገጥማቸውን እንግልት እንደሚያስቀር ገልጸዋል።
ፋይሎችን ዲጂታላይዝ የማድረጉ ተግባር እስከ ግንቦት ወር መጨረሻ በማጠናቀቅ ለዜጎች ፍትሃዊና ቀልጠፋ አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።
አሁን ላይ በሁሉም ክፍለ ከተሞች የመሬት ማኔጅመንት(ካዳስተር) ስራ ከፍተኛ በጀት ተመድቦ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመው በዚህም ስለከተማዋ መሬት የተሟላ መረጃ ማግኘት የሚቻልበት ሁኔታ ይፈጠራል ብለዋል።
በተጨማሪም የተቋም ግንባታ ላይ በማተኮር ከተማዋን ለቱሪዝም፣ ለኢንቨስትመንትና ለነዋሪዎች ምቹ ለማድረግ የኮሪደር ልማትን ጨምሮ ሌሎች የመሰረተ ልማት ዝርጋታዎች እየተከናወኑ እንደሆነም ገልፀዋል።
የባህር ዳር ከተማን ስማርት ሲቲ ማድረግን ታሳቢ ያደረጉ የልማትና የመልካም አስተዳደር ተግባራት በየዘርፉ እየተከናወኑ መሆኑን አመልክተዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026