የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በሐረሪ ክልል ለአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ ነው

May 8, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ለአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ መሆኑ ተገልጿል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ ሮዛ ዑመር በክልሉ የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ዝግጅትን አስመልክተው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ለመጪው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ላላቸው የችግኝ ዓይነቶች ትኩረት ተሰጥቷል።

በዚህም በዘንድሮው ክረምት ከሚተከሉ ችግኞች ውስጥ 70 በመቶው ለምግብነት የሚያገለግሉ የፍራፍሬና አትክልት ችግኞች ሲሆኑ 30 በመቶዎቹ ደግሞ የደን ችግኞች ናቸው ብለዋል።


በተለይም በክልሉ የሚታወቁና በአሁኑ ወቅት እየጠፉና በመጥፋት ላይ የሚገኙ እንደ አምባሾክ፣ ጊሽጣና ሌሎች ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ እንደሚገኝም አክለዋል።

ይህም የህብረተሰቡን ፍላጎት ታሳቢ በማድረግና የፍራፍሬ ዝርያዎችን ወደ ቀድሞ ሁኔታ ለመመለስ በማሰብ ተግባራዊ የተደረገ ነው ብለዋል።


በክልሉ በሚገኙ ሶስት የችግኝ ማዘጋጃ ጣቢያዎች ላይ ችግኝ የማዘጋጀቱ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ የተፈጥሮ ሃብት ዳይሬክተር አቶ አራርሶ አደም ናቸው።

ለተከላ የሚሆን ስፍራ የመለየት እና የማዘጋጀት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝና በዚህም ዘንድሮ በክልሉ በተለያዩ ስፍራዎች 1 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ችግኝ እንደሚተከል ተናግረዋል።

ባለፈው ክረምት በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር በተራቆቱ አካባቢዎች የተተከሉት ችግኞች በሚደረግላቸው እንክብካቤ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙም አመልክተዋል።


በክልሉ የጠፉና እየጠፉ የሚገኙ የፍራፍሬና የሐረር ቡና ችግኝን የማዘጋጀት ስራ ማጠናቀቃቸውንና የደንና የመኖ ችግኞችን እያዘጋጁ እንደሚገኙ የተናገሩት ደግሞ በቢሮው የችግኝ ጣቢያዎች ስራ ክትትልና ድጋፍ ባለሙያ አቶ ሻሜ ደሴ ናቸው።


የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስራ አካባቢን ወደ ለምለምነት ከመቀየር ባለፈ ለእኛም የስራ እድል ፈጥሮልናል፤ ችግኞቹም በወቅቱ እንዲደርሱ እያዘጋጀን እንገኛለን ያሉት የችግኝ ጣቢያ ሰራተኛ የሆኑት ወይዘሮ ዘምዘም አብዱራህማን ናቸው።


የችግኝ ዝግጅት ስራውን እያከናወኑ መሆኑን የተናገረችው ደግሞ ሌላዋ የችግኝ ጣቢያ ሰራተኛ ሰሚራ መሐመድ ናት።

በተለይ እንደ ከዚህ በፊቱ ከችግኝ ማዘጋጀቱ ጎን ለጎን በተከላው ስራ እንደምትሳተፍም ጨምራ ተናግራለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026