የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በሐረሪ ክልል ለአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ ነው

May 8, 2025

IDOPRESS

ሐረር፤ ሚያዝያ 29/2017(ኢዜአ)፦ በሐረሪ ክልል ለአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች እየተዘጋጁ መሆኑ ተገልጿል።

የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር እና የግብርና ልማት ቢሮ ኃላፊ ሮዛ ዑመር በክልሉ የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ዝግጅትን አስመልክተው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በክልሉ ለመጪው ክረምት የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ላላቸው የችግኝ ዓይነቶች ትኩረት ተሰጥቷል።

በዚህም በዘንድሮው ክረምት ከሚተከሉ ችግኞች ውስጥ 70 በመቶው ለምግብነት የሚያገለግሉ የፍራፍሬና አትክልት ችግኞች ሲሆኑ 30 በመቶዎቹ ደግሞ የደን ችግኞች ናቸው ብለዋል።


በተለይም በክልሉ የሚታወቁና በአሁኑ ወቅት እየጠፉና በመጥፋት ላይ የሚገኙ እንደ አምባሾክ፣ ጊሽጣና ሌሎች ችግኞችን የማዘጋጀት ስራ ትኩረት ተሰጥቶት እየተከናወነ እንደሚገኝም አክለዋል።

ይህም የህብረተሰቡን ፍላጎት ታሳቢ በማድረግና የፍራፍሬ ዝርያዎችን ወደ ቀድሞ ሁኔታ ለመመለስ በማሰብ ተግባራዊ የተደረገ ነው ብለዋል።


በክልሉ በሚገኙ ሶስት የችግኝ ማዘጋጃ ጣቢያዎች ላይ ችግኝ የማዘጋጀቱ ስራ እየተከናወነ መሆኑን የተናገሩት ደግሞ በክልሉ ግብርና ልማት ቢሮ የተፈጥሮ ሃብት ዳይሬክተር አቶ አራርሶ አደም ናቸው።

ለተከላ የሚሆን ስፍራ የመለየት እና የማዘጋጀት ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝና በዚህም ዘንድሮ በክልሉ በተለያዩ ስፍራዎች 1 ሺህ ሄክታር መሬት ላይ ችግኝ እንደሚተከል ተናግረዋል።

ባለፈው ክረምት በክልሉ በአረንጓዴ አሻራ ልማት መርሃ ግብር በተራቆቱ አካባቢዎች የተተከሉት ችግኞች በሚደረግላቸው እንክብካቤ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙም አመልክተዋል።


በክልሉ የጠፉና እየጠፉ የሚገኙ የፍራፍሬና የሐረር ቡና ችግኝን የማዘጋጀት ስራ ማጠናቀቃቸውንና የደንና የመኖ ችግኞችን እያዘጋጁ እንደሚገኙ የተናገሩት ደግሞ በቢሮው የችግኝ ጣቢያዎች ስራ ክትትልና ድጋፍ ባለሙያ አቶ ሻሜ ደሴ ናቸው።


የአረንጓዴ አሻራ ልማት ስራ አካባቢን ወደ ለምለምነት ከመቀየር ባለፈ ለእኛም የስራ እድል ፈጥሮልናል፤ ችግኞቹም በወቅቱ እንዲደርሱ እያዘጋጀን እንገኛለን ያሉት የችግኝ ጣቢያ ሰራተኛ የሆኑት ወይዘሮ ዘምዘም አብዱራህማን ናቸው።


የችግኝ ዝግጅት ስራውን እያከናወኑ መሆኑን የተናገረችው ደግሞ ሌላዋ የችግኝ ጣቢያ ሰራተኛ ሰሚራ መሐመድ ናት።

በተለይ እንደ ከዚህ በፊቱ ከችግኝ ማዘጋጀቱ ጎን ለጎን በተከላው ስራ እንደምትሳተፍም ጨምራ ተናግራለች።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026