የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ4 ቢሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር ተፈጽሟል-ሚኒስትር መላኩ አለበል

May 8, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 29/2017 (ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከ4 ቢሊዮን ብር በላይ የገበያ ትስስር መፈጠሩን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።


የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በሦስተኛው የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ማጠቃለያ መርሐግብር ላይ ባደረጉት ንግግር ማምረት የህልውና አጀንዳ ነው ብለዋል።


ሀገር አቀፍ የ2017 የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ ከመካሄዱ አስቀድሞ በክልሎች፣ በዞኖችና በወረዳዎች 168 የውይይት መድረኮች እና 94 የንግድ ትርኢቶች መካሄዳቸውን ገልጸው፤ በነዚህ የንግድ ትርኢቶቹ 400 ሚሊዮን ብር የሚገመት ግብይት መፈፀምንም ጠቅሰዋል።


ማምረት የህልውና አጀንዳ ነው ያሉት ሚኒስትሩ፥ የሀገር ውስጥ ምርትን ማስፋትና የመጠቀም ባህልን ለማሳደግ የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በተከታታይ እየተካሄደ ነው ብለዋል።


የኢትዮጵያ ታምርት የ2017 ኤክስፖ በርካታ አምራቾች ምርቶቻችን እንዳቀረቡበትና ከ120 ሺህ በላይ ጎብኝዎች እንደተሳተፉበትም ገልጸዋል።


በኤክስፖው ከ4 ቢሊዮን ብር በላይ ግብይትና ገበያ ትስስር መፈጸሙን ጠቅሰው፥ የዘርፉን ማነቆዎች ለመፍታት የሚያስችሉ የፓናል ውይይቶች እንደተካሄዱም አንስተዋል።


በኤክስፖው በምርት ብዛ፣ አይነትና በመጠን ከፍተኛ እድገት ተመዝግቧል ያሉት ሚኒስትሩ፥ የሀገር የፈጠራ አቅም የታየበት መድረክ መሆኑንም ተናግረዋል።


ኢትዮጵያ ከማሸለብ ዘመን ወጥታ በዕድገት ጎዳና እንድትጓዝ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ ጉልህ ሚና እየተጫወተ መሆኑንም ገልጸዋል።


ንቅናቄው የገጠር ኢንዱስትሪን ለመጀመር የሚያስችል ዕድል መፍጠሩን በማንሳት፥ የኢትዮጵያ ታምርት ኤክስፖ በመጪዎቹ ዓመታትም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።


በቀጣይ ዓመትም ከሚያዚያ 24 እስከ 28/2018 ዓ.ም ዓለም አቀፍ ደረጃውን ጠብቆ እንደሚካሄድ ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026