
ወልቂጤ፤ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የም ዞን ከ87 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የኮሾ አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ተገለፀ።
ፕሮጀክቱን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማእረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትራንስፖርት እና መንገድ ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑርዬ (ዶ/ር ) በይፋ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።
የመስኖ ፕሮጀክቱ የአርሶ አደሮችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማሳደግና ገበያ በማረጋጋት ረገድ ያለው ፋይዳ ከፍ ያለ መሆኑም ተገልጿል።
በክልሉ የመስኖ ተቋማት ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ካሳዬ ተክሌ፥ የመስኖ ፕሮጀክቱ ግንባታ በሳጃ ዙሪያ ወረዳ ዲቻ ቀበሌ በ2016 ዓ/ም አጋማሽ እንደተጀመረ ገልፀዋል።
በ87 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክቱ 600 የቤተሰብ መሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገልፀው፥ ለእንስሳት የመጠጥ ውሃ የሚሆን ቦታ ተካቶበት መገንባቱን ተናግረዋል።
በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይም የክልሉና የዞኑ አመራር አባላት እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026