የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በየም ዞን ከ87 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት በቃ

May 12, 2025

IDOPRESS

ወልቂጤ፤ግንቦት 2/2017(ኢዜአ)፦በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የም ዞን ከ87 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተገነባው የኮሾ አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክት ተመርቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ተገለፀ።


ፕሮጀክቱን በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማእረግ የመሰረተ ልማት ክላስተር አስተባባሪ እና የክልሉ ትራንስፖርት እና መንገድ ቢሮ ኃላፊ መሀመድ ኑርዬ (ዶ/ር ) በይፋ መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።


የመስኖ ፕሮጀክቱ የአርሶ አደሮችን የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማሳደግና ገበያ በማረጋጋት ረገድ ያለው ፋይዳ ከፍ ያለ መሆኑም ተገልጿል።


በክልሉ የመስኖ ተቋማት ልማትና አስተዳደር ኤጀንሲ ስራ አስኪያጅ ኢንጅነር ካሳዬ ተክሌ፥ የመስኖ ፕሮጀክቱ ግንባታ በሳጃ ዙሪያ ወረዳ ዲቻ ቀበሌ በ2016 ዓ/ም አጋማሽ እንደተጀመረ ገልፀዋል።


በ87 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር የተገነባው የመስኖ ፕሮጀክቱ 600 የቤተሰብ መሪዎችን ተጠቃሚ እንደሚያደርግ ገልፀው፥ ለእንስሳት የመጠጥ ውሃ የሚሆን ቦታ ተካቶበት መገንባቱን ተናግረዋል።


በምረቃ ስነ-ስርዓቱ ላይም የክልሉና የዞኑ አመራር አባላት እንዲሁም የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026