
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 4/2017(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ተኪ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በማምረት በኩል አበረታች ውጤቶች መመዝገባቸውን የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ አስታወቀ።
የቢሮው ምክትል ኃላፊ ተፈሪ ታረቀኝ ለኢዜአ እንዳሉት፥ በክልሉ ለኢንዱስትሪ ምርታማነት አቅም የሚሆን የማዕድንና የግብርና ምርት የግብዓት አቅርቦት በስፋት አለ።
በበጀት ዓመቱ ባለፉት ዘጠኝ ወራት የክልሉ አምራች ኢንዱስትሪዎች ከሀገር ውስጥ ባለፈ ጥራቱን የጠበቀ ምርት ለውጭ ገበያ ማቅረብ የቻሉበትን ስኬታማ አፈፃፀም ማስመዝገባቸውንም ተናግረዋል።
በዚህም 48 አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርቶቻቸውን ለውጭ ገበያ በማቅረብ የውጭ ምንዛሬ ገቢ ማስገኘታቸውን አስታውቀዋል።
የአምራች ኢንዱስትሪ ምርታማነት አቅሞችን በማሳደግ የሀገር ውስጥ ገበያ ፍላጎትን በራስ ምርት የመተካት ስራ ቁልፍ ተግባር መሆኑንም አንስተዋል።
በዚህም በክልሉ የኢንዱስትሪ ምርታማነት አቅሞችን በማጎልበት 630 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር የሚያወጣ የተኪ ምርት ስራ መሰራቱን አስረድተዋል።
በዘጠኝ ወራት ውስጥ 143 አዳዲስ ኢንዱስትሪዎች ወደ ስራ መግባታቸውን ጠቁመው፤ በሂደቱም ከ52 ሺህ በላይ ዜጎች ቋሚ የስራ ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄም የአሰራር ችግሮችን በመፍታትና አዳዲስ ኢንቨስትመንትን በመሳብ የክልሉን የኢንዱስትሪ ልማት እያነቃቃ እንደሚገኝ ገልጸዋል።
በዚህም በተኪና ወጪ ንግድ ምርት በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ገበያ ተወዳዳሪ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በማምረት እምርታዊ ውጤት መመዝገቡን ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በ2014 ዓ.ም ከተጀመረ አንስቶም ከ485 በላይ ኢንዱስትሪዎች በአዲስ መልክ ወደ ስራ በማስገባትበርካታ የአሰራር ማነቆዎችን ማስወገድ እንደተቻለም አስረድተዋል።
የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ባለሃብቶችም መዋዕለ ነዋያቸውን ፈሰስ በማድረግ በአማራ ክልል ያለው ምቹ የኢንቨስትመንት ዕድል እንዲጠቀሙ ጥሪ አቅርበዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026