የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የአርሶ አደሩን ምርታማነት ለማሳደግ ሙያዊ ድጋፋችንን አጠናክረን ቀጥለናል - የግብርና ባለሙያዎች

May 15, 2025

IDOPRESS

ሰቆጣ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፡- ለአካባቢው የሚስማሙ የሰብል ዝርያ ለይተው ለአርሶ አደሩ በማመቻቸትና የኩታ ገጠም አሰራርን እያበረታቱ ምርታማነትን ለማሳደግ ድጋፋቸውን አጠናክረው መቀጠላቸውን በዋግ ኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ሰቆጣ ወረዳ የግብርና ባለሙያዎች ተናገሩ።

በቅርቡም በቀበሌና በመንደር ደረጃ የአካባቢን ስነ ምህዳር መሰረት ያደረገ የሰብል ልማት የተግባር ተኮር ስልጠና ለግብርና ባለሙያዎችና አርሶ አደሮች መሰጠቱ ተመልክቷል።

ከስልጠናው ተሳታፊዎች መካከል በሰቆጣ ወረዳ የ02 ቀበሌ ግብርና ባለሙያ አቶ ቢራራ መለሰ በሰጡት አስተያየት ፤ በመጪው መኽር ሰብል ልማት ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ የሚያስችል ስራ እየተከናወነ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ለአካባቢው የሚስማሙ የሰብል ዝርያዎችን በመለየት፣ የሰው ሰራሽና የተፈጥሮ ማዳበሪያን በማቅረብና በኩታ ገጠም የመዝራት ዘዴን እያበረታቱ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚሁ ወረዳ የ020 ቀበሌ የግብርና ባለሙያ አቶ ባዬ መሰለ በበኩላቸው፤ በቅርቡ የተሰጠን ስልጠና የአካባበያችን ጸጋ አውቀን ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችል ነው ብለዋል።

ይህንን ውደ ተግባር በማሸጋገር ለአርሶ አደሩ የሚሰጡትን ሙያዊ ድገፍ ይበልጥ አጠናክረው የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ አበክረው እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በስልጠናው ከተሳታፉ የሰቆጣ ወረዳ 02 ቀበሌ ነዋሪዎች ውስጥ አርሶ አደር ማሞ መለሰ፤ የሰብል ልማታቸውን አስፋፍተው ምርታማነት ለማሳደግ ከስልጠናው የተሻለ እውቀትና ልምድ ማግኘታቸውን ገልጸዋል።

ስልጠናው ለአካባቢያቸው ተስማሚ የሆኑ የሰብል ዓይነቶችን ለይተን እንድናለማ የሚያስችል ነው ብለዋል።

አርሶ አደር ሲሳይ አያልነህ በበኩላቸው፤ ምርታማነትን ለማሳደግ የተፈጥሮና የሰው ሰራሽ ማዳበሪያ አጠቃቀም ስልት በአግባቡ መረዳት የቻልንበት ስልጠና ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ይህንን በመጠቀም በመጪው የመኽር ወቅት ሰብልን በኩታ ገጠም ለማልማት ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።


የብሔረሰብ አስተዳደሩ ግብርና መምሪያ ሃላፊ አቶ አዲስ ወልዴ ለኢዜአ እንደገለጹት ፤ በ2017/2018 የምርት ዘመን ምርታማነትን በማሳደግ ከተረጅነት ለመላቀቅ ትኩረት ተሰጥቷል።

በዚህም በመኸሩ ወቅት 120 ሺህ 638 ሄክታር መሬት በዘር ለመሸፈን ታቅዶ ወደ ተግባር መገባቱን አስታውቀዋል።

እስካሁን በሄክታር ከ7 ኩንታል የነበረውን ምርታማነት ወደ 13 ኩንታል ለማሳደግ ግብ ተይዞ እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል።

ይህም በምግብ ራስን ለመቻል፣ ለኢንዱስትሪ ግብዓት የሚሆኑና ለወጭ ንግድ የሚውሉ ገበያ ተኮር ሰብል ልማት ላይ በማተኮር ጭምር እንደሆነ ተናግረዋል።

ለዚህም ስኬታማነት ግብአት በወቅቱ በማቅረብና አዳዲስ ቴክኖሎጅዎችን በመተግበር ላይ መሆኑን ገልጸዋል።

በቅርቡም በቀበሌና በመንደር ደረጃ የአካባቢን ስነ ምህዳር መሰረት ያደረገ የሰብል ልማት የተግባር ተኮር ስልጠና ለግብርና ባለሙያዎችና አርሶ አደሮች መሰጠቱንም አውስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026