የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በጋምቤላ ክልል ያሉትን የተፈጥሮ ጸጋዎች አልምቶ ለመጠቀም የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ይጠናከራሉ - ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)

May 15, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ያሉትን የተፈጥሮ ጸጋዎች አልምቶ ለመጠቀም የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እንደሚጠናከሩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) ገለጹ።

"የክልሉ የገጠር መንገድ ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና" የተሰኘ ፕሮጀክት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ይፋዊ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የክልሉን የተፈጥሮ ጸጋዎች በአግባቡ አልምቶ ለመጠቀምና የተጀመረውን የልማት ስራዎችን ለማፋጠን የመንገድ መሰረተ ልማት ወሳኝ ነው።

በክልሉ ሰፊ ለም መሬት፣ ውሃ፣ ማዕድን፣ የቱሪዝም መዳረሻዎችና ሌሎች የተፈጥሮ ጸጋዎች እንዳሉ ጠቅሰው፤ እነዚህ ሀብቶች በተገቢው ለምተው ለህዝቡ ጥቅም ሳይውል እንዲቆይ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱ የመንገድ መሰረተ ልማት ክፈተት እንደሆነ አውስተዋል።


ሆኖም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ የመንግድ መሰረተ ልማት ችግሮች ለማቃለል በክልሉና በፌዴራል መንግስት በተደረገው ጥረት ውጤቶች መታየታቸውን ገልጸዋል።

የክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎችን ስኬታማ ለማድረግ የተጀመሩትን የመንገድ መስረተ ልማት ስራዎች አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል።

በተለይም ይፋ የተደረገው የገጠር መንገድ ትስስርና ተደራሽነት ፕሮጀክት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለመውጣት ለታለመው ግብ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።

ለፕሮጀክቱ ስኬታማነት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትብብር እንዲሰሩ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።


የክልሉ ገጠር መንገዶች ዋና ዳይሬክተር ኮማንዳር ኡማን ኡጋላ በበኩላቸው፤ መንገድ ለሁሉም የልማት ዘርፎች መሳለጥ ዓይነተኛ ድርሻ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይ አምስት ዓመታት የሚተገበረው ይኸው የገጠር መንገድ ትስስርና ተደረሽነት ፕሮጀክት ድልድዮችን ጨምሮ የገጠር አገናኝ መንገዶች ግንባታና ጥገና ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ ይሆናል ብለዋል።

ይህም ለአርሶ አደሩ የምርት ግብዓቶችን ለማቅረብና ምርቱን ወደ ገበያ ለማድረስ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025