
ጋምቤላ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ያሉትን የተፈጥሮ ጸጋዎች አልምቶ ለመጠቀም የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እንደሚጠናከሩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) ገለጹ።
"የክልሉ የገጠር መንገድ ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና" የተሰኘ ፕሮጀክት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ይፋዊ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።
ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የክልሉን የተፈጥሮ ጸጋዎች በአግባቡ አልምቶ ለመጠቀምና የተጀመረውን የልማት ስራዎችን ለማፋጠን የመንገድ መሰረተ ልማት ወሳኝ ነው።
በክልሉ ሰፊ ለም መሬት፣ ውሃ፣ ማዕድን፣ የቱሪዝም መዳረሻዎችና ሌሎች የተፈጥሮ ጸጋዎች እንዳሉ ጠቅሰው፤ እነዚህ ሀብቶች በተገቢው ለምተው ለህዝቡ ጥቅም ሳይውል እንዲቆይ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱ የመንገድ መሰረተ ልማት ክፈተት እንደሆነ አውስተዋል።

ሆኖም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ የመንግድ መሰረተ ልማት ችግሮች ለማቃለል በክልሉና በፌዴራል መንግስት በተደረገው ጥረት ውጤቶች መታየታቸውን ገልጸዋል።
የክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎችን ስኬታማ ለማድረግ የተጀመሩትን የመንገድ መስረተ ልማት ስራዎች አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል።
በተለይም ይፋ የተደረገው የገጠር መንገድ ትስስርና ተደራሽነት ፕሮጀክት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለመውጣት ለታለመው ግብ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።
ለፕሮጀክቱ ስኬታማነት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትብብር እንዲሰሩ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።

የክልሉ ገጠር መንገዶች ዋና ዳይሬክተር ኮማንዳር ኡማን ኡጋላ በበኩላቸው፤ መንገድ ለሁሉም የልማት ዘርፎች መሳለጥ ዓይነተኛ ድርሻ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።
በቀጣይ አምስት ዓመታት የሚተገበረው ይኸው የገጠር መንገድ ትስስርና ተደረሽነት ፕሮጀክት ድልድዮችን ጨምሮ የገጠር አገናኝ መንገዶች ግንባታና ጥገና ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ ይሆናል ብለዋል።
ይህም ለአርሶ አደሩ የምርት ግብዓቶችን ለማቅረብና ምርቱን ወደ ገበያ ለማድረስ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026