የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በጋምቤላ ክልል ያሉትን የተፈጥሮ ጸጋዎች አልምቶ ለመጠቀም የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች ይጠናከራሉ - ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር)

May 15, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ያሉትን የተፈጥሮ ጸጋዎች አልምቶ ለመጠቀም የመንገድ መሰረተ ልማት ስራዎች እንደሚጠናከሩ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን(ዶ/ር) ገለጹ።

"የክልሉ የገጠር መንገድ ትስስርና ተደራሽነት ለምግብ ዋስትና" የተሰኘ ፕሮጀክት ዛሬ በጋምቤላ ከተማ ይፋዊ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር ተካሂዷል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ በዚሁ ወቅት እንደተናገሩት፤ የክልሉን የተፈጥሮ ጸጋዎች በአግባቡ አልምቶ ለመጠቀምና የተጀመረውን የልማት ስራዎችን ለማፋጠን የመንገድ መሰረተ ልማት ወሳኝ ነው።

በክልሉ ሰፊ ለም መሬት፣ ውሃ፣ ማዕድን፣ የቱሪዝም መዳረሻዎችና ሌሎች የተፈጥሮ ጸጋዎች እንዳሉ ጠቅሰው፤ እነዚህ ሀብቶች በተገቢው ለምተው ለህዝቡ ጥቅም ሳይውል እንዲቆይ ካደረጉት ምክንያቶች አንዱ የመንገድ መሰረተ ልማት ክፈተት እንደሆነ አውስተዋል።


ሆኖም ባለፉት የለውጥ ዓመታት በክልሉ የመንግድ መሰረተ ልማት ችግሮች ለማቃለል በክልሉና በፌዴራል መንግስት በተደረገው ጥረት ውጤቶች መታየታቸውን ገልጸዋል።

የክልሉ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ የልማት ስራዎችን ስኬታማ ለማድረግ የተጀመሩትን የመንገድ መስረተ ልማት ስራዎች አጠናክሮ ማስቀጠል ያስፈልጋል ብለዋል።

በተለይም ይፋ የተደረገው የገጠር መንገድ ትስስርና ተደራሽነት ፕሮጀክት የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ከተረጂነት ለመውጣት ለታለመው ግብ ፋይዳው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል።

ለፕሮጀክቱ ስኬታማነት ሁሉም ባለድርሻ አካላት በትብብር እንዲሰሩ ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ አሳስበዋል።


የክልሉ ገጠር መንገዶች ዋና ዳይሬክተር ኮማንዳር ኡማን ኡጋላ በበኩላቸው፤ መንገድ ለሁሉም የልማት ዘርፎች መሳለጥ ዓይነተኛ ድርሻ ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

በቀጣይ አምስት ዓመታት የሚተገበረው ይኸው የገጠር መንገድ ትስስርና ተደረሽነት ፕሮጀክት ድልድዮችን ጨምሮ የገጠር አገናኝ መንገዶች ግንባታና ጥገና ስራዎች ላይ ትኩረት አድርጎ የሚሰራ ይሆናል ብለዋል።

ይህም ለአርሶ አደሩ የምርት ግብዓቶችን ለማቅረብና ምርቱን ወደ ገበያ ለማድረስ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር መሆኑን ገልጸዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026