የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የምግብ ዋስትናችንን ከማረጋገጥ ባሻገር ለገበያ የሚሆን ምርት ለማግኘት እየሰራን ነው-አርሶ አደሮች

May 15, 2025

IDOPRESS

ደብረብርሃን ፤ግንቦት 6/2017 (ኢዜአ)፡- በመጪው የመኸር ወቅት የምግብ ዋስትናችንን ከማረጋገጥ ባሻገር ለገበያ የሚሆን ምርት ለማምረት ከወዲሁ እየሰራን ነው ሲሉ በሰሜን ሸዋ ዞን የሚገኙ አርሶ አደሮች ገለጹ።

የዞኑ ግብርና መምሪያ በበኩሉ በ2017/18 ምርት ዘመን መኸር ወቅት በሰብል ከሚለማው መሬት 20 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰበሰብ አቅዶ እየሰራ መሆኑን አመላክቷል።

በዞኑ ባሶና ወራና ወረዳ የጊፍት ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ንጉሱ አጥላው ለኢዜአ እንደገለጹት በመጪው ክረምት መኽር ወቅት በአንድ ሄክታር ከሩብ መሬታቸው ላይ ስንዴ፣ ጤፍና ባቄላ ለመዝራት ወስነዋል።

መሬታቸውን እስከ ሶስት ጊዜ ደጋግመው በማረስና ምርታማነትን በማሳደግ በምግብ ራሳቸውን ከመቻል ባለፈ ለገበያ የሚሆን ምርት ለማምረት ከወዲሁ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

በተጨማሪም የምርት ማሳደጊያ ማዳበሪያና ምርጥ ዘርን በመጠቀም ምርታማነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን አስረድተዋል።


ሌላዋ አርሶ አደር ትርንጎ ግርማ በበኩላቸው በምርት ወቅቱ ግማሽ ሄክታር ማሳቸውን በስንዴና ጤፍ ዘር ለመሸፈን መሬታቸውን ደጋግመው በማረስ ለዘር ማዘጋጀታቸውን ተናግረዋል።

የዘንድሮ የማዳበሪያ አቅርቦት ቀደም ብሎ በመከናወኑ በእርሻ ስራቸው ላይ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን ጠቁመው የምግብ ዋስትናቸውን ከማረጋገጥ ያለፈ ለገበያ የሚሆን ምርት ለማምረት ከወዲሁ ከማሳ ዝግጅት ጀምሮ እየተጉ መሆኑን ተናግረዋል።


በሰሜን ሸዋ ዞን ግብርና መምሪያ የሰብል ልማት ቡድን መሪ አቶ አበበ ጌታቸው በበኩላቸው በመጪው የመኸር ወቅት 556 ሺህ 800 ሄክታር መሬት በተለያዩ ሰብሎች በዘር ለመሸፈን እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

እስካሁን በተደረገው ጥረት 449 ሺህ 157 ሄክታር መሬት በድግግሞሽ ታርሶ ለዘር ዝግጁ መሆኑን ጠቁመው ከዚህ ውስጥ 43 ሺህ 385 ሄክታር መሬት በትራክተር የታረሰ መሆኑን አመልክተዋል።

በእቅድ ከተያዘው ከግማሽ በላይ የሚሆነው መሬት በኩታ ገጠም የአስተራረስ ዘዴና ሌሎች አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችንና አሰራሮችን በመጠቀም እንደሚከናወን አስረድተዋል።

"በአሲድ የተጠቃውን መሬት በኖራ በማከምና ዘመናዊ ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በመጠቀም በመጪው መኸር 20 ነጥብ 1 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰበሰብ ግብ ተይዞ እየተሰራ ነው" ብለዋል።

በመኸር ወቅቱ አርሶ አደሩ በምግብ ራስን ከመቻል ባሻገር ለኢንዱስትሪ ግብዓትና፣ ለወጪ ንግድ የሚሆኑ ምርቶች ላይ እንዲያተኩር እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026