ድሬዳዋ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ የፕሮጀክቶች ግንባታ በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የክትትልና ቁጥጥር ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ገለጸ።
የባለስልጣኑ አመራሮች እና ባለሙያዎች በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እየተገነቡ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲውን የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል፣ የመምህራን መኖሪያ ህንፃዎች እና በዋና ጊቢው እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በሰነድና በመስክ ገምግመዋል።
የባለስልጣኑ የቁጥጥር ዘርፍ ኃላፊ ደረጀ አረጋኸኝ፤ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት የግንባታ ፕሮጀክቶች በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
በዚሁ ረገድ ተቋሙ በመላው ሀገሪቱ የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የክትትልና ቁጥጥር ሥራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በጥሩ ሂደት ላይ መሆናቸውን አስተውለናል ያሉት ኃላፊው በተለይም የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታሉን እንዲሁም የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ግንባታ በዚህ ዓመት ማጠናቀቅ የሚያስችል ደረጃ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ለፕሮጀክቶቹ በጥራትና በተለያዘላቸው ጊዜ መጠናቀቅ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ክትትል ድጋፍና ቁጥጥር እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ ጊዚያት በፕሮጀክቶች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን አስቀድሞ መፍታት የሚያስችሉ ሳይንሳዊ ጥናቶች አስጠንቶ ወደ ስራ እንደሚያስገባም ጠቁመዋል።
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንትፊክ ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ገደፋይ(ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርስቲው እየተከናወኑ የሚገኙ የግንባታ ፕሮጀክቶች በፍጥነት እና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የባለስልጣኑ መስሪያ ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች በአካል በመገኘት የሚያደርጉት ክትትልና ድጋፍ ለፕሮጀክቶቹ መፋጠን ወሳኝ ሚና ማበርከቱንም አንስተዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025