የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የፕሮጀክቶች ግንባታ በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የክትትልና ቁጥጥር ስራው ተጠናክሮ ይቀጥላል - ባለስልጣኑ

May 15, 2025

IDOPRESS

ድሬዳዋ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ የፕሮጀክቶች ግንባታ በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የክትትልና ቁጥጥር ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ገለጸ።

የባለስልጣኑ አመራሮች እና ባለሙያዎች በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እየተገነቡ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲውን የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል፣ የመምህራን መኖሪያ ህንፃዎች እና በዋና ጊቢው እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በሰነድና በመስክ ገምግመዋል።

የባለስልጣኑ የቁጥጥር ዘርፍ ኃላፊ ደረጀ አረጋኸኝ፤ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት የግንባታ ፕሮጀክቶች በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

በዚሁ ረገድ ተቋሙ በመላው ሀገሪቱ የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የክትትልና ቁጥጥር ሥራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በጥሩ ሂደት ላይ መሆናቸውን አስተውለናል ያሉት ኃላፊው በተለይም የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታሉን እንዲሁም የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ግንባታ በዚህ ዓመት ማጠናቀቅ የሚያስችል ደረጃ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

ለፕሮጀክቶቹ በጥራትና በተለያዘላቸው ጊዜ መጠናቀቅ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ክትትል ድጋፍና ቁጥጥር እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።

ባለስልጣኑ በቀጣይ ጊዚያት በፕሮጀክቶች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን አስቀድሞ መፍታት የሚያስችሉ ሳይንሳዊ ጥናቶች አስጠንቶ ወደ ስራ እንደሚያስገባም ጠቁመዋል።

የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንትፊክ ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ገደፋይ(ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርስቲው እየተከናወኑ የሚገኙ የግንባታ ፕሮጀክቶች በፍጥነት እና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

የባለስልጣኑ መስሪያ ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች በአካል በመገኘት የሚያደርጉት ክትትልና ድጋፍ ለፕሮጀክቶቹ መፋጠን ወሳኝ ሚና ማበርከቱንም አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026