
ድሬዳዋ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ የፕሮጀክቶች ግንባታ በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የክትትልና ቁጥጥር ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ገለጸ።
የባለስልጣኑ አመራሮች እና ባለሙያዎች በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እየተገነቡ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲውን የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል፣ የመምህራን መኖሪያ ህንፃዎች እና በዋና ጊቢው እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በሰነድና በመስክ ገምግመዋል።
የባለስልጣኑ የቁጥጥር ዘርፍ ኃላፊ ደረጀ አረጋኸኝ፤ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት የግንባታ ፕሮጀክቶች በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
በዚሁ ረገድ ተቋሙ በመላው ሀገሪቱ የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የክትትልና ቁጥጥር ሥራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በጥሩ ሂደት ላይ መሆናቸውን አስተውለናል ያሉት ኃላፊው በተለይም የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታሉን እንዲሁም የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ግንባታ በዚህ ዓመት ማጠናቀቅ የሚያስችል ደረጃ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ለፕሮጀክቶቹ በጥራትና በተለያዘላቸው ጊዜ መጠናቀቅ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ክትትል ድጋፍና ቁጥጥር እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ ጊዚያት በፕሮጀክቶች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን አስቀድሞ መፍታት የሚያስችሉ ሳይንሳዊ ጥናቶች አስጠንቶ ወደ ስራ እንደሚያስገባም ጠቁመዋል።
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንትፊክ ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ገደፋይ(ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርስቲው እየተከናወኑ የሚገኙ የግንባታ ፕሮጀክቶች በፍጥነት እና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የባለስልጣኑ መስሪያ ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች በአካል በመገኘት የሚያደርጉት ክትትልና ድጋፍ ለፕሮጀክቶቹ መፋጠን ወሳኝ ሚና ማበርከቱንም አንስተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026