
ድሬዳዋ፤ ግንቦት 6/2017(ኢዜአ)፦ የፕሮጀክቶች ግንባታ በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የክትትልና ቁጥጥር ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን ገለጸ።
የባለስልጣኑ አመራሮች እና ባለሙያዎች በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እየተገነቡ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲውን የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታል፣ የመምህራን መኖሪያ ህንፃዎች እና በዋና ጊቢው እየተከናወኑ የሚገኙ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በሰነድና በመስክ ገምግመዋል።
የባለስልጣኑ የቁጥጥር ዘርፍ ኃላፊ ደረጀ አረጋኸኝ፤ በዚሁ ጊዜ እንዳሉት የግንባታ ፕሮጀክቶች በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ በልዩ ትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
በዚሁ ረገድ ተቋሙ በመላው ሀገሪቱ የሚከናወኑ ፕሮጀክቶች በጥራት፣ በፍጥነት እና በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ የክትትልና ቁጥጥር ሥራ እያከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ እየተገነቡ የሚገኙ ፕሮጀክቶች በጥሩ ሂደት ላይ መሆናቸውን አስተውለናል ያሉት ኃላፊው በተለይም የማስተማሪያና ሪፈራል ሆስፒታሉን እንዲሁም የመምህራን መኖሪያ ቤቶች ግንባታ በዚህ ዓመት ማጠናቀቅ የሚያስችል ደረጃ ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ለፕሮጀክቶቹ በጥራትና በተለያዘላቸው ጊዜ መጠናቀቅ ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አስፈላጊውን ክትትል ድጋፍና ቁጥጥር እንደሚያደርግም አረጋግጠዋል።
ባለስልጣኑ በቀጣይ ጊዚያት በፕሮጀክቶች ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን አስቀድሞ መፍታት የሚያስችሉ ሳይንሳዊ ጥናቶች አስጠንቶ ወደ ስራ እንደሚያስገባም ጠቁመዋል።
የድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንትፊክ ዳይሬክተር ቴዎድሮስ ገደፋይ(ዶ/ር) በበኩላቸው በዩኒቨርስቲው እየተከናወኑ የሚገኙ የግንባታ ፕሮጀክቶች በፍጥነት እና በጥራት ተጠናቀው ለአገልግሎት እንዲበቁ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
የባለስልጣኑ መስሪያ ቤት አመራሮችና ባለሙያዎች በአካል በመገኘት የሚያደርጉት ክትትልና ድጋፍ ለፕሮጀክቶቹ መፋጠን ወሳኝ ሚና ማበርከቱንም አንስተዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026