
ቴፒ፤ግንቦት 7/2017 (ኢዜአ)፦በቴፒ ከተማ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ከ5 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር በላይ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስተዳደሩ አስታወቀ።
የከተማዋ ነዋሪዎች በበኩላቸው፥ ለልማቱ ስኬታማነት የበኩላቸውን ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የቴፒ ከተማ ከንቲባ አቶ ወንድሙ ግርማ እንደገለጹት፥በከተማዋ በመጀመሪያ ዙር በአስተዳደሩና በነዋሪዎች ተሳትፎ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ በሚበልጥ ወጪ ከ5 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር በላይ ኮሪደር ለማልማት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።
ልማቱ የእግረኛ መንገድ፣ የመንገድ አካፋይ፣መናፈሻ፣ ፏፏቴና የመንገድ ዳር መብራቶች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑንና ስራውም እየተፋጠነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
በከተማዋ የኮሪደር ልማቱ ወደስራ የገባው ከህብረተሰቡ ጋር መግባባት ላይ ከተደረሰ በኋላ መሆኑን ያነሱት ከንቲባው፥ የከተማዋ ነዋሪዎች ንብረታቸውን ከማንሳት ጀምሮ በተለያየ መንገድ ድጋፍና ትብብር እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል መምህር ሰሎሞን ይትባረክ፣ በከተማዋ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ ለከተማዋ ውበት ከመሆኑ ባለፈ እድገቷን እንደሚያፋጥነው ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራው እንዲፋጠን ከአስተዳደሩ ጋር በመቀናጀት በገንዘብ፣በሀሳብና በጉልበት የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑንም ገልጸዋል።
የተለያዩ ከተሞችን የኮሪደር ልማት ሥራ እንደተመለከቱና ወደ ቴፒ ከተማም ልማቱ እንዲመጣ ሲመኙ እንደነበር የተናገሩት ደግሞ አቶ ጌታቸው ደለለኝ የተባሉ ነዋሪ ናቸው።
ከኮሪደር ልማቱ ባሻገር የአስፋልት መንገድ በከተማዋ መጀመሩ ለዕድገቷ ተጨማሪ እድል ይዞ ይመጣል ያሉት ደግሞ አቶ ታከለ ዘውዴ የተባሉ ነዋሪ ናቸው።
የልማት ሥራ በመንግስት ብቻ የሚከናወን እንዳልሆነ ገልጸው፥ ለኮሪደር ልማቱ ስኬታማነቱ የሚጠበቅባቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በኮሪደር ልማቱ የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው የከተማዋ ወጣቶች መካከል ኢሳይያስ ቆጭቶ ነገ የተሻለች ከተማ የማየት ተስፋ ይዞ እየሠራ መሆኑን ተናግሯል።
እየተፋጠነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ ሲጠናቀቅ የከተማዋን ገጽታ ይቀይራል የሚል እምት እንዳለው ገልጾ፥ በልማቱ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱንም ተናግሯል።
የቴፒ ከተማ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከአራቱ ብዝኃ ዋና ከተሞች አንዷ ናት።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026