የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በቴፒ ከተማ ከ5 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር በላይ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ ነው

May 16, 2025

IDOPRESS

ቴፒ፤ግንቦት 7/2017 (ኢዜአ)፦በቴፒ ከተማ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ከ5 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር በላይ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስተዳደሩ አስታወቀ።


የከተማዋ ነዋሪዎች በበኩላቸው፥ ለልማቱ ስኬታማነት የበኩላቸውን ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የቴፒ ከተማ ከንቲባ አቶ ወንድሙ ግርማ እንደገለጹት፥በከተማዋ በመጀመሪያ ዙር በአስተዳደሩና በነዋሪዎች ተሳትፎ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ በሚበልጥ ወጪ ከ5 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር በላይ ኮሪደር ለማልማት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።


ልማቱ የእግረኛ መንገድ፣ የመንገድ አካፋይ፣መናፈሻ፣ ፏፏቴና የመንገድ ዳር መብራቶች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑንና ስራውም እየተፋጠነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።


በከተማዋ የኮሪደር ልማቱ ወደስራ የገባው ከህብረተሰቡ ጋር መግባባት ላይ ከተደረሰ በኋላ መሆኑን ያነሱት ከንቲባው፥ የከተማዋ ነዋሪዎች ንብረታቸውን ከማንሳት ጀምሮ በተለያየ መንገድ ድጋፍና ትብብር እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።


ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል መምህር ሰሎሞን ይትባረክ፣ በከተማዋ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ ለከተማዋ ውበት ከመሆኑ ባለፈ እድገቷን እንደሚያፋጥነው ተናግረዋል።


የኮሪደር ልማት ሥራው እንዲፋጠን ከአስተዳደሩ ጋር በመቀናጀት በገንዘብ፣በሀሳብና በጉልበት የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑንም ገልጸዋል።


የተለያዩ ከተሞችን የኮሪደር ልማት ሥራ እንደተመለከቱና ወደ ቴፒ ከተማም ልማቱ እንዲመጣ ሲመኙ እንደነበር የተናገሩት ደግሞ አቶ ጌታቸው ደለለኝ የተባሉ ነዋሪ ናቸው።


ከኮሪደር ልማቱ ባሻገር የአስፋልት መንገድ በከተማዋ መጀመሩ ለዕድገቷ ተጨማሪ እድል ይዞ ይመጣል ያሉት ደግሞ አቶ ታከለ ዘውዴ የተባሉ ነዋሪ ናቸው።


የልማት ሥራ በመንግስት ብቻ የሚከናወን እንዳልሆነ ገልጸው፥ ለኮሪደር ልማቱ ስኬታማነቱ የሚጠበቅባቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።


በኮሪደር ልማቱ የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው የከተማዋ ወጣቶች መካከል ኢሳይያስ ቆጭቶ ነገ የተሻለች ከተማ የማየት ተስፋ ይዞ እየሠራ መሆኑን ተናግሯል።


እየተፋጠነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ ሲጠናቀቅ የከተማዋን ገጽታ ይቀይራል የሚል እምት እንዳለው ገልጾ፥ በልማቱ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱንም ተናግሯል።


የቴፒ ከተማ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከአራቱ ብዝኃ ዋና ከተሞች አንዷ ናት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026