
ቴፒ፤ግንቦት 7/2017 (ኢዜአ)፦በቴፒ ከተማ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ከ5 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር በላይ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስተዳደሩ አስታወቀ።
የከተማዋ ነዋሪዎች በበኩላቸው፥ ለልማቱ ስኬታማነት የበኩላቸውን ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የቴፒ ከተማ ከንቲባ አቶ ወንድሙ ግርማ እንደገለጹት፥በከተማዋ በመጀመሪያ ዙር በአስተዳደሩና በነዋሪዎች ተሳትፎ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ በሚበልጥ ወጪ ከ5 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር በላይ ኮሪደር ለማልማት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።
ልማቱ የእግረኛ መንገድ፣ የመንገድ አካፋይ፣መናፈሻ፣ ፏፏቴና የመንገድ ዳር መብራቶች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑንና ስራውም እየተፋጠነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
በከተማዋ የኮሪደር ልማቱ ወደስራ የገባው ከህብረተሰቡ ጋር መግባባት ላይ ከተደረሰ በኋላ መሆኑን ያነሱት ከንቲባው፥ የከተማዋ ነዋሪዎች ንብረታቸውን ከማንሳት ጀምሮ በተለያየ መንገድ ድጋፍና ትብብር እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል መምህር ሰሎሞን ይትባረክ፣ በከተማዋ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ ለከተማዋ ውበት ከመሆኑ ባለፈ እድገቷን እንደሚያፋጥነው ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራው እንዲፋጠን ከአስተዳደሩ ጋር በመቀናጀት በገንዘብ፣በሀሳብና በጉልበት የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑንም ገልጸዋል።
የተለያዩ ከተሞችን የኮሪደር ልማት ሥራ እንደተመለከቱና ወደ ቴፒ ከተማም ልማቱ እንዲመጣ ሲመኙ እንደነበር የተናገሩት ደግሞ አቶ ጌታቸው ደለለኝ የተባሉ ነዋሪ ናቸው።
ከኮሪደር ልማቱ ባሻገር የአስፋልት መንገድ በከተማዋ መጀመሩ ለዕድገቷ ተጨማሪ እድል ይዞ ይመጣል ያሉት ደግሞ አቶ ታከለ ዘውዴ የተባሉ ነዋሪ ናቸው።
የልማት ሥራ በመንግስት ብቻ የሚከናወን እንዳልሆነ ገልጸው፥ ለኮሪደር ልማቱ ስኬታማነቱ የሚጠበቅባቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በኮሪደር ልማቱ የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው የከተማዋ ወጣቶች መካከል ኢሳይያስ ቆጭቶ ነገ የተሻለች ከተማ የማየት ተስፋ ይዞ እየሠራ መሆኑን ተናግሯል።
እየተፋጠነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ ሲጠናቀቅ የከተማዋን ገጽታ ይቀይራል የሚል እምት እንዳለው ገልጾ፥ በልማቱ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱንም ተናግሯል።
የቴፒ ከተማ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከአራቱ ብዝኃ ዋና ከተሞች አንዷ ናት።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026