ቴፒ፤ግንቦት 7/2017 (ኢዜአ)፦በቴፒ ከተማ በህብረተሰቡ ተሳትፎ ከ5 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር በላይ የኮሪደር ልማት ሥራ እየተከናወነ መሆኑን አስተዳደሩ አስታወቀ።
የከተማዋ ነዋሪዎች በበኩላቸው፥ ለልማቱ ስኬታማነት የበኩላቸውን ድጋፍ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል።
የቴፒ ከተማ ከንቲባ አቶ ወንድሙ ግርማ እንደገለጹት፥በከተማዋ በመጀመሪያ ዙር በአስተዳደሩና በነዋሪዎች ተሳትፎ ከ80 ሚሊዮን ብር በላይ በሚበልጥ ወጪ ከ5 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር በላይ ኮሪደር ለማልማት ሥራ እየተከናወነ ይገኛል።
ልማቱ የእግረኛ መንገድ፣ የመንገድ አካፋይ፣መናፈሻ፣ ፏፏቴና የመንገድ ዳር መብራቶች ግንባታ እየተከናወነ መሆኑንና ስራውም እየተፋጠነ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
በከተማዋ የኮሪደር ልማቱ ወደስራ የገባው ከህብረተሰቡ ጋር መግባባት ላይ ከተደረሰ በኋላ መሆኑን ያነሱት ከንቲባው፥ የከተማዋ ነዋሪዎች ንብረታቸውን ከማንሳት ጀምሮ በተለያየ መንገድ ድጋፍና ትብብር እያደረጉ መሆኑን ገልጸዋል።
ከከተማዋ ነዋሪዎች መካከል መምህር ሰሎሞን ይትባረክ፣ በከተማዋ የተጀመረው የኮሪደር ልማት ሥራ ለከተማዋ ውበት ከመሆኑ ባለፈ እድገቷን እንደሚያፋጥነው ተናግረዋል።
የኮሪደር ልማት ሥራው እንዲፋጠን ከአስተዳደሩ ጋር በመቀናጀት በገንዘብ፣በሀሳብና በጉልበት የበኩላቸውን እየተወጡ መሆኑንም ገልጸዋል።
የተለያዩ ከተሞችን የኮሪደር ልማት ሥራ እንደተመለከቱና ወደ ቴፒ ከተማም ልማቱ እንዲመጣ ሲመኙ እንደነበር የተናገሩት ደግሞ አቶ ጌታቸው ደለለኝ የተባሉ ነዋሪ ናቸው።
ከኮሪደር ልማቱ ባሻገር የአስፋልት መንገድ በከተማዋ መጀመሩ ለዕድገቷ ተጨማሪ እድል ይዞ ይመጣል ያሉት ደግሞ አቶ ታከለ ዘውዴ የተባሉ ነዋሪ ናቸው።
የልማት ሥራ በመንግስት ብቻ የሚከናወን እንዳልሆነ ገልጸው፥ ለኮሪደር ልማቱ ስኬታማነቱ የሚጠበቅባቸውን እየተወጡ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በኮሪደር ልማቱ የሥራ ዕድል ከተፈጠረላቸው የከተማዋ ወጣቶች መካከል ኢሳይያስ ቆጭቶ ነገ የተሻለች ከተማ የማየት ተስፋ ይዞ እየሠራ መሆኑን ተናግሯል።
እየተፋጠነ ያለው የኮሪደር ልማት ሥራ ሲጠናቀቅ የከተማዋን ገጽታ ይቀይራል የሚል እምት እንዳለው ገልጾ፥ በልማቱ የኢኮኖሚ ተጠቃሚ እየሆነ መምጣቱንም ተናግሯል።
የቴፒ ከተማ ከደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል ከአራቱ ብዝኃ ዋና ከተሞች አንዷ ናት።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025