አዲስ አበባ፤ግንቦት 8/2017(ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የሳይበር ደህንነት ምህዳርን የሚያጠናክሩ ቁልፍ የዲጅታል መሰረተ ልማቶችን መገንባቷን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ ገለጹ።
በምስራቅ አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነው የኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ ኤክስፖ በአዲስ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን ማዕከል በይፋ ተከፍቷል።
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ በዚሁ ወቅት፥ቴክኖሎጂ የሁሉ ነገር መሰረት እየሆነ መምጣቱን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታውን በቅጡ በመገንዘብና ቴክኖሎጂ ለሀገር ሁለንተናዊ ልማት ያለውን ፋይዳ በመረዳት ዲጂታል መሰረተ ልማትን እያስፋፋች ነው ብለዋል።
ብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ፣የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ የሥልጠና ኢኒሼቲቭ እንዲሁም የመንግሥት አገልግሎቶችን ወደ ዲጂታል የማስገባት ስራዎች እየተከናወኑ እንደሚገኙም አንስተዋል።
የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ የሚያስችሉ ቁልፍ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች መገንባታቸውን ያነሱት ዋና ዳይሬክተሯ፥ በስማርት ሲቲ ግንባታም ለሌሎች ሀገራት ምሳሌ የሚሆኑ ተግባራት እየተከናወኑ ነው ብለዋል።
አካታች ኢኮኖሚ ለመገንባትና አገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመን ቴክኖሎጂ የማይተካ ሚና እንዳለውና ይህን የበለጠ ማሳደግ ላይ በትኩረት እየተሠራ መሆኑንም ገልጸዋል።
የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች የሳይበር ደህንነት ካውንስል ሊቀመንበር መሃመድ አልኩዋቲ (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ቴክኖሎጂ ዓለምን የመቀየር ትልቅ አቅም እንዳለው አንስተዋል።
የሳይበር ደህንነትን ማረጋገጥ የብሄራዊ ደህንነትን ሉዓላዊነት ማረጋገጥ መሆኑን ጠቅሰው፥ በዚህ ላይ ሀገራት በትኩረት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
ከቴክኖሎጂ ዕድገት ጋር ተያይዞ የሚከሰቱ የሳይበር ደህንነት ስጋቶችን ለመቀነስ ትብብርን ማጠናከርና ተለዋዋጭ የሳይበር ደህንነት ስጋትን ታሳቢ ያደረገ አቅም መገንባት ወሳኝ እንደሆነም ጠቁመዋል።
የቴክኖሎጂ ኤክስፖው እስከ ግንቦት 10/2017 ዓ.ም የሚቆይ ሲሆን የበርካታ ሀገራት ግዙፍ የቴክኖሎጂ ኩባንያዎችና ከአስር ሺህ በላይ ተሳታፊዎች እየተሳተፉበት ነው።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025