
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 9/2018(ኢዜአ)፦በሀገር በቀል ፈጠራ የተቃኘ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ በአፍሪካ ለሚስተዋሉ ዘርፍ ተሻጋሪ ችግሮች ሁነኛ መፍትሄ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ተናገሩ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) “አርቲፊሻል ኢንተሊጀንስን ለአፍሪካ ብልጽግና እና ትብብር” በሚል ጭብጥ እየተካሄደ ባለው “አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ለአፍሪካ” መርሃ-ግብር በመገኘት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በመልዕክታቸውም አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ለአፍሪካ የምርጫ ጉዳይ እንዳልሆነ አስረድተዋል።
በአፍሪካ የሚስተዋሉ ዘርፍ ተሻጋሪ ችግሮችን ትርጉም ባለው መልኩ ማቃለል የሚቻለው በሀገር በቀል ፈጠራ በተቃኘ የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሆኑንም ነው የተናገሩት።

አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ አካባቢን፣ ማህበረሰብንና ዘርፎችን የሚሻገር የለውጥ ሞተር መሆኑን ጠቅሰው፤ አህጉሪቱን እየፈተኑ ያሉ ችግሮችን ለመፍታት ሁነኛ አማራጭ መሆኑንም አብራርተዋል።
አፍሪካም ዘርፉን በተመለከተ አካታችነትንና የክህሎት ልማትን የሚያፋጥኑ ወሳኝ የፖሊሲ እርምጃዎችን በመተግበር የመሪነት ሚናዋን መወጣት እንዳለባትም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አፅንኦት ሰጥተዋል።
የዲጂታል ስርዓትን ለማስፋት በሚከናወኑ ስራዎች የመረጃ ሉዓላዊነትን ማስከበር ትኩረት ሊሰጠው እንደሚገባ ተናግረዋል።

ይህም በውጭ ቴክኖሎጂዎች ላይ ያለንን ጥገኝነት ለመከላከል ያስችለናል ብለዋል።
ከዚህ አኳያ ኢትዮጵያም በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በዲጂታል መሠረተ ልማትና የክሂሎት ማበልጸጊያ ሥራዎች በአርዓያነት እየመራች መሆኑን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ ከአምስት ዓመታት በፊት የአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ ኢንስቲትዩት አቋቁማ ወደ ስራ መግባቷንም ጠቅሰዋል።

ኢትዮጵያ በታዳሽ ሃይል ልማትና ቴሌኮም ዘርፍ ያከናወነችው ስራም ለዲጂታል ምህዳሩ መስፋት አይነተኛ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ጠቅሰዋል።
እንደ ዲጂታል መታወቂያ እንዲሁም የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭ ያሉ መርሃ ግብሮችም ኢትዮጵያ ሕልሞችን ወደ ተጨባጭ ተግባር እያሸጋገረች መሆኗን ማሳያ መሆናቸውንም አንስተዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026