
አዲስ አበባ፤ግንቦት 8/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው እና በወጭ ንግዱ ላይ በተከናወነው የቁጥጥር ስራ ከቁም እንስሳት እንዲሁም ስጋና ወተት የሚገኘውን ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ እያሳደገው እንደሚገኝ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ስርዓቱ የተረጋጋ፣ ፍትሐዊና ተደራሽ እንዲሆን እንዲሁም የወጪና ገቢ ምርቶች ጥራታቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ የማረጋገጥ ተግባር በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ወንድሙ ፍላቴ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያ ቁም እንስሳት፣ ስጋና የወተት ምርቶችን ለውጭ ገበያ በማቅረብ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ በማግኘት ላይ ትገኛለች፡፡
በዘርፉ በተከናወኑ ከፍተኛ ስራዎችም በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 406 ሺህ የቁም እንስሳትና 23 ሺህ 986 ቶን የስጋና ወተት ምርት በመላክ 128 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል፡፡
በቁም እንስሳት፣በስጋና ወተት እንዲሁም በመኖ ዘርፍ ለማግኘት የታቀደው ዕቅድ አፈጻጸም ከባለፈው አመት ሲነጻጸር በሁሉም መስክ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
ይህም ለውጥ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የዶላር ምንዛሬ በገበያ እንዲወሰንና ላኪያዎችን ማበረታታቱ እንዲሁም በወጪና ገቢ ምርቶች ላይ የሚደረገው የምርት ጥራት ቁጥጥር ምክንያት የመጣ መሆኑን ተናግረዋል።
በሀገሪቱ ወጪና ገቢ ምርቶች ጥራት በመቆጣጠር የጥራት ማረጋገጫ ከሚሰጡ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን አንዱ ነው።
የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሀሚድ ጀማል በበኩላቸው፤ በዓለም ገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ መሆን የሚቻለው የምርት ጥራትና ደህንነት መጠበቅ ሲቻል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
በዚህም ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ የቁም እንስሳትና ስጋ ምርቶች ጥራታቸውና ደህንነታቸው የጠበቁ ስለመሆናቸው ማረጋገጫ የመስጠት ተግባር እያከናወኑ መሆኑን አብራርተዋል።
በዚህም በህገ ወጥ መንገድ ሲወጡ የነበሩ እንስሳት በህጋዊ መንገድ እንዲወጡ ማስቻሉን አመላክተዋል።
የኢትዮጵያ ስጋ አምራችና ላኪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ከሊፋ ሁሴን ፤ በዓለም ገበያ ውስጥ መዳረሻን ለማስፋትና ተወዳዳሪ ለመሆን ጥራት ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን ጠቅሰው፥ማህበራቱ በዓለም አቀፍ የተቀመጡ የጥራት ደረጃን ተግባራዊ በማድረግ ላይ መሆናቸውን አብራርተዋል።
የምርት ጥራትን መጠበቅ በዓለም ገበያ ውስጥ ተወዳዳሪነትን የሚጨምር ከመሆኑም ባለፈ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የሚታደርገውን ጥረት የሚደግፍ መሆኑም ተገልጿል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026