የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ከስጋና ከወተት የሚገኘውን ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ እያሳደገው ነው-ንግድና ቀጣናዊ ሚኒስቴር

May 19, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 8/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ ተግባራዊ የተደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው እና በወጭ ንግዱ ላይ በተከናወነው የቁጥጥር ስራ ከቁም እንስሳት እንዲሁም ስጋና ወተት የሚገኘውን ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ እያሳደገው እንደሚገኝ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የንግድ ስርዓቱ የተረጋጋ፣ ፍትሐዊና ተደራሽ እንዲሆን እንዲሁም የወጪና ገቢ ምርቶች ጥራታቸውን የጠበቁ እንዲሆኑ የማረጋገጥ ተግባር በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡


የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር ወንድሙ ፍላቴ ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ኢትዮጵያ ቁም እንስሳት፣ ስጋና የወተት ምርቶችን ለውጭ ገበያ በማቅረብ ከዘርፉ የውጭ ምንዛሬ በማግኘት ላይ ትገኛለች፡፡


በዘርፉ በተከናወኑ ከፍተኛ ስራዎችም በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት 406 ሺህ የቁም እንስሳትና 23 ሺህ 986 ቶን የስጋና ወተት ምርት በመላክ 128 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘት መቻሉን ተናግረዋል፡፡


በቁም እንስሳት፣በስጋና ወተት እንዲሁም በመኖ ዘርፍ ለማግኘት የታቀደው ዕቅድ አፈጻጸም ከባለፈው አመት ሲነጻጸር በሁሉም መስክ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡


ይህም ለውጥ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው የዶላር ምንዛሬ በገበያ እንዲወሰንና ላኪያዎችን ማበረታታቱ እንዲሁም በወጪና ገቢ ምርቶች ላይ የሚደረገው የምርት ጥራት ቁጥጥር ምክንያት የመጣ መሆኑን ተናግረዋል።


በሀገሪቱ ወጪና ገቢ ምርቶች ጥራት በመቆጣጠር የጥራት ማረጋገጫ ከሚሰጡ ተቋማት መካከል የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን አንዱ ነው።


የኢትዮጵያ ግብርና ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሀሚድ ጀማል በበኩላቸው፤ በዓለም ገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ መሆን የሚቻለው የምርት ጥራትና ደህንነት መጠበቅ ሲቻል መሆኑን ጠቁመዋል፡፡


በዚህም ለውጭ ገበያ የሚቀርቡ የቁም እንስሳትና ስጋ ምርቶች ጥራታቸውና ደህንነታቸው የጠበቁ ስለመሆናቸው ማረጋገጫ የመስጠት ተግባር እያከናወኑ መሆኑን አብራርተዋል።


በዚህም በህገ ወጥ መንገድ ሲወጡ የነበሩ እንስሳት በህጋዊ መንገድ እንዲወጡ ማስቻሉን አመላክተዋል።


የኢትዮጵያ ስጋ አምራችና ላኪዎች ማህበር ፕሬዝዳንት ከሊፋ ሁሴን ፤ በዓለም ገበያ ውስጥ መዳረሻን ለማስፋትና ተወዳዳሪ ለመሆን ጥራት ቅድሚያ የሚሰጠው መሆኑን ጠቅሰው፥ማህበራቱ በዓለም አቀፍ የተቀመጡ የጥራት ደረጃን ተግባራዊ በማድረግ ላይ መሆናቸውን አብራርተዋል።


የምርት ጥራትን መጠበቅ በዓለም ገበያ ውስጥ ተወዳዳሪነትን የሚጨምር ከመሆኑም ባለፈ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የሚታደርገውን ጥረት የሚደግፍ መሆኑም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026