የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኢትዮጵያ አስቻይ የህግ ማዕቀፎች ተግባራዊ መደረጋቸው ዲጂታል ኢትዮጵያ በመገንባት ሂደት ተጨባጭ ውጤት አምጥቷል

May 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦በኢትዮጵያ አስቻይ የህግ ማዕቀፎችና ቅንጅታዊ አሰራሮች ተግባራዊ መደረጋቸው ዲጂታል ኢትዮጵያን በመገንባት ሂደት ተጨባጭ ውጤት እንዲመዘገብ ማስቻሉን የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር በለጠ ሞላ (ዶ/ር) ገለጹ።


የአይዲ ፎር አፍሪካ አለምአቀፍ አመታዊ ጉባኤ በኢትዮጵያ መካሄድ ጀምሯል።


ጉባኤው የብሄራዊ ዲጂታል መታወቂያ ለአካታች ዕድገት ያለውን ጠቀሜታና የአገራት አተገባበር ላይ የልምድ ልውውጥ የሚደረግበት ነው።


ኢትዮጵያም የዲጂታል መታወቂያ ትግበራዋን ለጉባኤው ተሳታፊዎች አቅርባለች።


የኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስትሩ በለጠ ሞላ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ኢትዮጵያ ዲጂታል መታወቂያን ተግባራዊ ለማድረግ የህግ ማዕቀፎችን ከማዘጋጀት ጀምሮ የተለያዩ የፖሊሲና ስትራቴጂ በማዘጋጀት ወደ ስራ ገብታለች።


በተለይም ለዲጂታል መታወቂያ መደላድል የሚፈጥሩ የዲጂታል መሰረተ ልማቶች ግንባታ በመንግስት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት መሰራቱንም አመልክተዋል።


በ2025 ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ የዲጂታል ፖሊሲና ስትራቴጂ ተነድፎ ወደ ትግበራ መገባቱን ነው የተናገሩት።


ባለፋት አምስት ዓመታት የተከናወኑ ስራዎች ዲጂታል ፖሊሲና ስትራቴጂ በመቅረጽ ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ያነሱት ሚኒስትሩ፤ ዲጂታል መታወቂያ ፕሮግራምን ተግባራዊ ለማድረግ የነበረውን ዝግጅትና ቁርጠኝነት አብራርተዋል።


የዲጂታላይዜሽን ግንባታ ሂደት እንጂ አንዴ የሚጠናቀቅ ስራ አለመሆኑን ጠቅሰዋል።


ለዲጂታል ትራንስፎርሜሽን እውን ማድረግ አስቻይ ሁኔታዎችን ከመፍጠር ባለፈ የመንግስት ተቋማት በቅንጅት እየሰሩ መሆኑንም አንስተዋል።


በዚህም የመንግስትን አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ የማስተሳሰርና የአገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍናን ማረጋገጥ መቻሉንም ጠቅሰዋል።


በዚህ ረገድም ዲጂታል መታወቂያ ለፋይናንስ አካታችነት ወሳኝ ሚና እየተጫወተ መሆኑን ጠቅሰው፥ በተለይም በገጠር አካባቢ ያሉ ዜጎች የፋይናንስ አገልግሎትን በቀላሉ እንዲያገኙ ማስቻሉን አንስተዋል።


የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ትዕግስት ሀሚድ በበኩላቸው፥ የዲጂታል ኢትዮጵያ ካውንስል ስራዎችን አብራርተዋል።


በዚህም ካውንስሉ ከመንግስት ተቋማት ባለፈ የግል ዘርፉን በማሳተፍ የተለያዩ ተግባራት እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።


የአምስት ሚሊዮን ኮደርስ ኢኒሼቲቭን በማስተባበር በርካታ ዜጎች ዲጂታላይዜሽን ላይ መሰረታዊ ግንዛቤ እንዲኖራቸው እየተደረገ መሆኑንም ገልጸዋል።


የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ምዝገባና ነዋሪነት አገልግሎን ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር ዮናስ አለማየሁ፤ አዲስ አበባን ስማርት ሲቲ ለማድረግ እየተከናወነ ላለው ተግባር የዲጂታል መታወቂያ ተደራሽነት ትልቅ ድርሻ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።


በከተማዋ የተለያዩ መሰረተ ልማቶችን ከማሟላት ባለፈ የዲጂታል መታወቂያ ላይ ትርጉም ያለው ስራ ተሰርቷል ብለዋል።


የልደት፣ የሞትና ሌሎች ወሳኝ ኩነቶችን በአጭር ጊዜ በመመዝገብ ዲጂታል ማንነትን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026