ጅማ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ ባለፋት ዓመታት የተከናወነው የተቀናጀ አደጋ መከላከል እና መልሶ ማቋቋም ሥራ ውጤት የተመዘገበበት መሆኑን የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) አስታወቁ።
በጅማ ከተማ በሌማት ትሩፉትና የምግብ ስርዓት ሽግግር እንዲሁም የአደጋ ሥራ አመራር ግምገማና የቀጣይ አቅጣጫ ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሂዷል።
በመድረኩ የተገኙት የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር)፤ ባለፉት ዓመታት በተደረገ የተቀናጀ አደጋን የመከላከል ሥራ ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል።
በዚህም ከአራት ዓመት በፊት የነበረው የድጋፍ ፈላጊ ቀጥርን በከፍተኛ ሁኔታ ዝቅ ማድረግ መቻሉን ገልጸው፣ ተፈናቃዮችንም የመመለስ ሥራ በስፋት መከናወኑን ተናግረዋል።
ለአደጋ ጊዜ ፈጥኖ መድረስ እንዲቻል የመጠባበቂያ የምግብ ክምችት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ለዚሁ ይረዳ ዘንድ የክምችት አቅምን ለማሳድግ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።
በየደረጃው ባሉ አመራሮች አስተባባሪነት እንደ ሀገር 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ምግብና የምግብ ነክ ክምችት ለመያዝ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንም አንስተዋል።
የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን ለመከላከልና ፈጥኖ ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ በራስ አቅም የተገነባ የትብብርና የቅንጅት ስራ እንደሚጠናከርም አመልክተዋል።
በተለያየ ጊዜ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋ የደረሰባቸውን ወገኖች በዘላቂነት ማቋቋም የሚያስችሉ እንቅስቃሴዎች ሲደረጉ መቆየታቸውንም ኮሚሽነሩ አክለዋል።
በተለይም ህብረተሰቡ እርዳታ ጠባቂ እንዳይሆንና ሰርቶ መለወጥ እንዲችል የግንዛቤ ማሳደጊያ ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ገልጸው፣ ለዚህም ሁኔታዎች እንዲመቻቹ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል።
አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...
Feb 28, 2025
ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...
Feb 28, 2025
አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...
Feb 12, 2025
አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...
Feb 8, 2025