
ጅማ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ ባለፋት ዓመታት የተከናወነው የተቀናጀ አደጋ መከላከል እና መልሶ ማቋቋም ሥራ ውጤት የተመዘገበበት መሆኑን የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር) አስታወቁ።
በጅማ ከተማ በሌማት ትሩፉትና የምግብ ስርዓት ሽግግር እንዲሁም የአደጋ ሥራ አመራር ግምገማና የቀጣይ አቅጣጫ ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሂዷል።
በመድረኩ የተገኙት የኢትዮጵያ የአደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም(ዶ/ር)፤ ባለፉት ዓመታት በተደረገ የተቀናጀ አደጋን የመከላከል ሥራ ተጨባጭ ውጤት መገኘቱን ገልጸዋል።
በዚህም ከአራት ዓመት በፊት የነበረው የድጋፍ ፈላጊ ቀጥርን በከፍተኛ ሁኔታ ዝቅ ማድረግ መቻሉን ገልጸው፣ ተፈናቃዮችንም የመመለስ ሥራ በስፋት መከናወኑን ተናግረዋል።
ለአደጋ ጊዜ ፈጥኖ መድረስ እንዲቻል የመጠባበቂያ የምግብ ክምችት አስፈላጊ መሆኑ ታምኖበት ለዚሁ ይረዳ ዘንድ የክምችት አቅምን ለማሳድግ ርብርብ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል።

በየደረጃው ባሉ አመራሮች አስተባባሪነት እንደ ሀገር 1 ነጥብ 5 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ምግብና የምግብ ነክ ክምችት ለመያዝ እንቅስቃሴ እየተደረገ መሆኑንም አንስተዋል።
የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን ለመከላከልና ፈጥኖ ሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረስ በራስ አቅም የተገነባ የትብብርና የቅንጅት ስራ እንደሚጠናከርም አመልክተዋል።
በተለያየ ጊዜ የተፈጥሮ እና ሰው ሰራሽ አደጋ የደረሰባቸውን ወገኖች በዘላቂነት ማቋቋም የሚያስችሉ እንቅስቃሴዎች ሲደረጉ መቆየታቸውንም ኮሚሽነሩ አክለዋል።
በተለይም ህብረተሰቡ እርዳታ ጠባቂ እንዳይሆንና ሰርቶ መለወጥ እንዲችል የግንዛቤ ማሳደጊያ ስራዎች ሲከናወኑ መቆየታቸውን ገልጸው፣ ለዚህም ሁኔታዎች እንዲመቻቹ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተሰራ ነው ብለዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026