የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ

በግብርናው ዘርፍ የሚከናወኑ ጥናትና ምርምሮች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

May 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ ግብርናውን በማዘመን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን ለማጎልበት በጥናትና ምርምር እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።

የዩኒቨርሲቲው አመታዊ የምርምር ሳምንት “መጻኢውን እንመግብ፣ በኢትዮጵያ ዘላቂ የምግብ ዋስትናን ከአዳዲስ ቴክኖሎጂና ፈጠራዎች ጋር ማስተሳሰር” በሚል መሪ ሃሳብ ቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው የእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ ተጀምሯል።

የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ወራሽ ጌታነህ በመክፈቻ መርሃ-ግብሩ እንዳሉት ኢትዮጵያ በምግብ እራሷን ለመቻል እያከናወነች ያለውን ተግባር ለሚደግፉ የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ትኩረት ተሰጥቷል።


የግብርናው ዘርፍ በሀገር ምጣኔ ሃብት እድገት፣ በስራ እድል ፈጠራና ምግብ ዋስትና ያለውን ጉልህ ሚና የበለጠ ለማሳደግ በምርምርና ቴክኖሎጂ መደገፍ ተገቢ መሆኑንም ገልጸዋል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በምርምር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ ተሳትፎ ቅድሚያ ከሰጣቸው ስምንት የምርምር አጀንዳዎች መካከል የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው ከበጀቱ እስከ 10 በመቶ ለምርምርና ፈጠራ ለማዋል እየሰራ እንደሚገኝም ጨምረው ገልጸዋል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንደ ሀገር ግብርናውን በማሸጋገር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተተገበሩ የሚገኙ መርሃ ግብሮችን እውን ለማድረግ በጥናትና ምርምር እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።


በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ ዋና ዲን ሒካ ዋቅቶሌ(ዶ/ር) በበኩላቸው ኮሌጁ ኢትዮጵያ ያላትን የእንስሳት ሃብት በአግባቡ ጥቅም ላይ እንድታውል ዩኒቨርሲቲው ምርምሩን እያሰፋ ይገኛል ብለዋል።


ድህነትን ለማጥፋትና ርሃብን ለማስወገድ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ምርምርና ፈጠራ ትልቁን ሚና እንደሚጫወቱ የተናገሩት ደግሞ በኢትዮጵያ የአለም የምግብና እርሻ ድርጅት የቴክኒክ አማካሪ ጀምስ ብዊራኒ ናቸው።

ኢትዮጵያ የግብርናውን ዘርፍ ምርትና ምርታማነት ለመጨመር ተግባራዊ ያደረገቻቸው የቴክኖሎጂና ምርምር ውጤቶች ወደ ውጭ የምትልካቸው ምርቶች መጨመር መቻሏ የሚበረታታ ነው ብለዋል።


በምርምር ሳምንቱ የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለጎብኚዎች ካቀረቡት መካከል በእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ የእንስሳት ጤና ባለሙያ ከፍ ያለው ሚደቅሳ በአካባቢው የእንስት ጤናን በመጠበቅ እየተሰሩ የሚገኙ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

የጥናትና ምርምር ሳምንቱ የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለጎብኚዎች በማቅረብ እስከ ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

<p>ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው</p>

አሶሳ፤ የካቲት 20/2017(ኢዜአ):- ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የትውልዱ አሻራና ኩራት ነው ሲሉ የአሶሳ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አብዱልሙህሲን ሐሰን...

Feb 28, 2025

<p>በተሰማራንበት መስክ ውጤታማ በመሆናችን ወደ መካከለኛ ኢንተርፕራይዝ ማደግ ችለናል</p>

ሚዛን አማን፤የካቲት 20/2017 (ኢዜአ)፦በቤንች ሸኮ ዞን ሚዛን አማን ከተማ በማህበር ተደራጅተው በተለያዩ የሥራ ዘርፎች የተሰማሩ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ በመ...

Feb 28, 2025

<p>ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው-ቋሚ ኮሚቴዎቹ</p>

አዲስ አበባ፤የካቲት 4 /2017(ኢዜአ)፦ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ በግብርናው ዘርፍ እያከናወነ ያለው በምርምር የተደገፈ ስራ ምሳሌ የሚሆን ነው ሲሉ የሕዝብ ተወካዮች ም...

Feb 12, 2025

<p>የማዕከሉ መገንባት በክልሉ የሚስተዋለውን የምርጥ ዘር ችግር በዘላቂነት ይቀርፋል - ኢንጂነር ነጋሽ ዋጌሾ (ዶ/ር)</p>

አዲስ አበባ፤ የካቲት 1/2017(ኢዜአ)፡- የቦንጋ የተቀናጀ የግብርና ግብዓትና ሜካናይዜሽን አገልግሎት ማዕከል መገንባት በክልሉ ለግብርና ስራው መሠረታዊ የሆነ...

Feb 8, 2025