
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ ግብርናውን በማዘመን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን ለማጎልበት በጥናትና ምርምር እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።
የዩኒቨርሲቲው አመታዊ የምርምር ሳምንት “መጻኢውን እንመግብ፣ በኢትዮጵያ ዘላቂ የምግብ ዋስትናን ከአዳዲስ ቴክኖሎጂና ፈጠራዎች ጋር ማስተሳሰር” በሚል መሪ ሃሳብ ቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው የእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ ተጀምሯል።
የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ወራሽ ጌታነህ በመክፈቻ መርሃ-ግብሩ እንዳሉት ኢትዮጵያ በምግብ እራሷን ለመቻል እያከናወነች ያለውን ተግባር ለሚደግፉ የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ትኩረት ተሰጥቷል።

የግብርናው ዘርፍ በሀገር ምጣኔ ሃብት እድገት፣ በስራ እድል ፈጠራና ምግብ ዋስትና ያለውን ጉልህ ሚና የበለጠ ለማሳደግ በምርምርና ቴክኖሎጂ መደገፍ ተገቢ መሆኑንም ገልጸዋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በምርምር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ ተሳትፎ ቅድሚያ ከሰጣቸው ስምንት የምርምር አጀንዳዎች መካከል የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል።
ዩኒቨርሲቲው ከበጀቱ እስከ 10 በመቶ ለምርምርና ፈጠራ ለማዋል እየሰራ እንደሚገኝም ጨምረው ገልጸዋል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንደ ሀገር ግብርናውን በማሸጋገር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተተገበሩ የሚገኙ መርሃ ግብሮችን እውን ለማድረግ በጥናትና ምርምር እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ ዋና ዲን ሒካ ዋቅቶሌ(ዶ/ር) በበኩላቸው ኮሌጁ ኢትዮጵያ ያላትን የእንስሳት ሃብት በአግባቡ ጥቅም ላይ እንድታውል ዩኒቨርሲቲው ምርምሩን እያሰፋ ይገኛል ብለዋል።

ድህነትን ለማጥፋትና ርሃብን ለማስወገድ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ምርምርና ፈጠራ ትልቁን ሚና እንደሚጫወቱ የተናገሩት ደግሞ በኢትዮጵያ የአለም የምግብና እርሻ ድርጅት የቴክኒክ አማካሪ ጀምስ ብዊራኒ ናቸው።
ኢትዮጵያ የግብርናውን ዘርፍ ምርትና ምርታማነት ለመጨመር ተግባራዊ ያደረገቻቸው የቴክኖሎጂና ምርምር ውጤቶች ወደ ውጭ የምትልካቸው ምርቶች መጨመር መቻሏ የሚበረታታ ነው ብለዋል።

በምርምር ሳምንቱ የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለጎብኚዎች ካቀረቡት መካከል በእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ የእንስሳት ጤና ባለሙያ ከፍ ያለው ሚደቅሳ በአካባቢው የእንስት ጤናን በመጠበቅ እየተሰሩ የሚገኙ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
የጥናትና ምርምር ሳምንቱ የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለጎብኚዎች በማቅረብ እስከ ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይም ተገልጿል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026