የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በግብርናው ዘርፍ የሚከናወኑ ጥናትና ምርምሮች ተጠናክረው ይቀጥላሉ - አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

May 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 11/2017(ኢዜአ)፦ ግብርናውን በማዘመን የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራትን ለማጎልበት በጥናትና ምርምር እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስታወቀ።

የዩኒቨርሲቲው አመታዊ የምርምር ሳምንት “መጻኢውን እንመግብ፣ በኢትዮጵያ ዘላቂ የምግብ ዋስትናን ከአዳዲስ ቴክኖሎጂና ፈጠራዎች ጋር ማስተሳሰር” በሚል መሪ ሃሳብ ቢሾፍቱ ከተማ በሚገኘው የእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ ተጀምሯል።

የዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሮፌሰር ወራሽ ጌታነህ በመክፈቻ መርሃ-ግብሩ እንዳሉት ኢትዮጵያ በምግብ እራሷን ለመቻል እያከናወነች ያለውን ተግባር ለሚደግፉ የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶች ትኩረት ተሰጥቷል።


የግብርናው ዘርፍ በሀገር ምጣኔ ሃብት እድገት፣ በስራ እድል ፈጠራና ምግብ ዋስትና ያለውን ጉልህ ሚና የበለጠ ለማሳደግ በምርምርና ቴክኖሎጂ መደገፍ ተገቢ መሆኑንም ገልጸዋል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በምርምር፣ ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህበረሰብ ተሳትፎ ቅድሚያ ከሰጣቸው ስምንት የምርምር አጀንዳዎች መካከል የመጀመሪያው መሆኑን ተናግረዋል።

ዩኒቨርሲቲው ከበጀቱ እስከ 10 በመቶ ለምርምርና ፈጠራ ለማዋል እየሰራ እንደሚገኝም ጨምረው ገልጸዋል።

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንደ ሀገር ግብርናውን በማሸጋገር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እየተተገበሩ የሚገኙ መርሃ ግብሮችን እውን ለማድረግ በጥናትና ምርምር እያከናወነ ያለውን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።


በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ ዋና ዲን ሒካ ዋቅቶሌ(ዶ/ር) በበኩላቸው ኮሌጁ ኢትዮጵያ ያላትን የእንስሳት ሃብት በአግባቡ ጥቅም ላይ እንድታውል ዩኒቨርሲቲው ምርምሩን እያሰፋ ይገኛል ብለዋል።


ድህነትን ለማጥፋትና ርሃብን ለማስወገድ የተቀመጡ የዘላቂ ልማት ግቦችን ለማሳካት ምርምርና ፈጠራ ትልቁን ሚና እንደሚጫወቱ የተናገሩት ደግሞ በኢትዮጵያ የአለም የምግብና እርሻ ድርጅት የቴክኒክ አማካሪ ጀምስ ብዊራኒ ናቸው።

ኢትዮጵያ የግብርናውን ዘርፍ ምርትና ምርታማነት ለመጨመር ተግባራዊ ያደረገቻቸው የቴክኖሎጂና ምርምር ውጤቶች ወደ ውጭ የምትልካቸው ምርቶች መጨመር መቻሏ የሚበረታታ ነው ብለዋል።


በምርምር ሳምንቱ የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለጎብኚዎች ካቀረቡት መካከል በእንስሳት ህክምና እና ግብርና ኮሌጅ የእንስሳት ጤና ባለሙያ ከፍ ያለው ሚደቅሳ በአካባቢው የእንስት ጤናን በመጠበቅ እየተሰሩ የሚገኙ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

የጥናትና ምርምር ሳምንቱ የምርምርና ቴክኖሎጂ ውጤቶችን ለጎብኚዎች በማቅረብ እስከ ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚቆይም ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026