
ጅማ፣ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፡- መንግስት ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ለሚያስችሉ ተግባራት ትኩረት መስጠቱን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕእረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለጹ።
ዓለም አቀፍ የንብ ቀንና 2ኛው ዘላቂ የንብ ማነብና እጽዋት ተራክቦ ኮንፈረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በተለይም ዓለም አቀፍ የንብ ቀን "ንቦችን እንጠብቅ" በሚል መሪ ሀሳብ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት እየተከበረ ነው።
አቶ አደም ፋራህ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር ፤ መንግስት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ።
የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብርም ዋንኛ አቅጣጫ ተደርጎ እየተተገበረ መሆኑን ጠቁመው፤ መርሃ-ግብሩ ለንብ ማነብና ለማር ምርታማነት እያበረከተ ያለውን አሰተዋጽኦ ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱንም አስታውቀዋል ።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በበኩላቸው አካባቢን በመንከባከብ የንቦችን ደህንነት በመጠበቅ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በንብ መንጋ ብዛትና በማር ምርት ከአፍሪካ አንደኛ መሆኗን ጠቅሰው ዘርፉ በዘመናዊ የማር አመራረት እየተለወጠ ነው ብለዋል።
የማር አመራረትን ለማዘመን በተሰጠው ትኩረት ባለፉት ዘጠኝ ወራት እንደ ሀገር 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዘመናዊ ቀፎ መሰራጨቱንና 250ሺህ ቶን የማር ምርት መገኘቱን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ በእንስሳት ሀብቷና በተፈጥሮ በታደለችው የአየር ጸባይ ለማር ምርት ምቹ በመሆኗ ከዘርፉ የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን በትጋት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026