የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ይገኛል

May 21, 2025

IDOPRESS

ጅማ፣ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፡- መንግስት ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ለሚያስችሉ ተግባራት ትኩረት መስጠቱን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕእረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለጹ።

ዓለም አቀፍ የንብ ቀንና 2ኛው ዘላቂ የንብ ማነብና እጽዋት ተራክቦ ኮንፈረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው።

በተለይም ዓለም አቀፍ የንብ ቀን "ንቦችን እንጠብቅ" በሚል መሪ ሀሳብ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት እየተከበረ ነው።

አቶ አደም ፋራህ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር ፤ መንግስት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ።

የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብርም ዋንኛ አቅጣጫ ተደርጎ እየተተገበረ መሆኑን ጠቁመው፤ መርሃ-ግብሩ ለንብ ማነብና ለማር ምርታማነት እያበረከተ ያለውን አሰተዋጽኦ ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱንም አስታውቀዋል ።


የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በበኩላቸው አካባቢን በመንከባከብ የንቦችን ደህንነት በመጠበቅ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ በንብ መንጋ ብዛትና በማር ምርት ከአፍሪካ አንደኛ መሆኗን ጠቅሰው ዘርፉ በዘመናዊ የማር አመራረት እየተለወጠ ነው ብለዋል።

የማር አመራረትን ለማዘመን በተሰጠው ትኩረት ባለፉት ዘጠኝ ወራት እንደ ሀገር 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዘመናዊ ቀፎ መሰራጨቱንና 250ሺህ ቶን የማር ምርት መገኘቱን አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ በእንስሳት ሀብቷና በተፈጥሮ በታደለችው የአየር ጸባይ ለማር ምርት ምቹ በመሆኗ ከዘርፉ የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን በትጋት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በክልሉ ምቹ የኢንቨስትመንት አካባቢ መፍጠር ዋነኛው የትኩረት አቅጣጫ ነው

ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...

Apr 23, 2026

በድሬዳዋ አስተዳደር አምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረት አቅማቸው ጨምሯል

ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...

Apr 17, 2026

የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ተሰጥቷል

ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...

Apr 1, 2026

የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር የልማት አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...

Mar 26, 2026