
ጅማ፣ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፡- መንግስት ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ለሚያስችሉ ተግባራት ትኩረት መስጠቱን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕእረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለጹ።
ዓለም አቀፍ የንብ ቀንና 2ኛው ዘላቂ የንብ ማነብና እጽዋት ተራክቦ ኮንፈረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በተለይም ዓለም አቀፍ የንብ ቀን "ንቦችን እንጠብቅ" በሚል መሪ ሀሳብ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት እየተከበረ ነው።
አቶ አደም ፋራህ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር ፤ መንግስት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ።
የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብርም ዋንኛ አቅጣጫ ተደርጎ እየተተገበረ መሆኑን ጠቁመው፤ መርሃ-ግብሩ ለንብ ማነብና ለማር ምርታማነት እያበረከተ ያለውን አሰተዋጽኦ ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱንም አስታውቀዋል ።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በበኩላቸው አካባቢን በመንከባከብ የንቦችን ደህንነት በመጠበቅ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በንብ መንጋ ብዛትና በማር ምርት ከአፍሪካ አንደኛ መሆኗን ጠቅሰው ዘርፉ በዘመናዊ የማር አመራረት እየተለወጠ ነው ብለዋል።
የማር አመራረትን ለማዘመን በተሰጠው ትኩረት ባለፉት ዘጠኝ ወራት እንደ ሀገር 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዘመናዊ ቀፎ መሰራጨቱንና 250ሺህ ቶን የማር ምርት መገኘቱን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ በእንስሳት ሀብቷና በተፈጥሮ በታደለችው የአየር ጸባይ ለማር ምርት ምቹ በመሆኗ ከዘርፉ የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን በትጋት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
ሀዋሳ ፤ሚያዝያ 14/2018 (ኢዜአ)፡-በሲዳማ ክልል ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራሮችን በመዘርጋት በርካታ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ወደ ክልሉ በመሳብ የዜጎችን ተጠቃ...
Apr 23, 2026
ድሬዳዋ፤ ሚያዝያ 9/2018 (ኢዜአ)፦ በሀገራዊ ለውጡ ለአምራች ኢንዱስትሪዎች የተሰጠው ትኩረት በአስተዳደሩ የአምራች ኢንዱስትሪዎች ተኪና ወጪ ምርቶችን የማምረ...
Apr 17, 2026
ጅግጅጋ፣መጋቢት 22/2018 (ኢዜአ)፡- መንግሥት የከተሞችን እድገትና የነዋሪዎችን ኑሮ ለማሻሻል ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ መሆኑ ተመለከተ። የኢትዮጵያ ከተሞች የ...
Apr 1, 2026
አዲስ አበባ፤ መጋቢት 16/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የኃይል አቅርቦት ስኬት ቀጣናዊ ትስስርን በማፋጠን የጋራ ብልፅግናን የሚያበስር አህጉራዊ የልማት አጀንዳ ...
Mar 26, 2026