
ጅማ፣ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፡- መንግስት ምርታማነትን በማሳደግ የዜጎችን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ ለሚያስችሉ ተግባራት ትኩረት መስጠቱን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕእረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊና የብልጽግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ አደም ፋራህ ገለጹ።
ዓለም አቀፍ የንብ ቀንና 2ኛው ዘላቂ የንብ ማነብና እጽዋት ተራክቦ ኮንፈረንስ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው።
በተለይም ዓለም አቀፍ የንብ ቀን "ንቦችን እንጠብቅ" በሚል መሪ ሀሳብ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት እየተከበረ ነው።
አቶ አደም ፋራህ በወቅቱ ባደረጉት ንግግር ፤ መንግስት የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥና ምርታማነትን ለማሳደግ የሚያስችሉ ተግባራት ላይ በትኩረት እየሰራ ነው ።
የሌማት ትሩፋት መርሃ-ግብርም ዋንኛ አቅጣጫ ተደርጎ እየተተገበረ መሆኑን ጠቁመው፤ መርሃ-ግብሩ ለንብ ማነብና ለማር ምርታማነት እያበረከተ ያለውን አሰተዋጽኦ ይበልጥ ለማጠናከር ከፍተኛ ትኩረት መሰጠቱንም አስታውቀዋል ።

የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ(ዶ/ር) በበኩላቸው አካባቢን በመንከባከብ የንቦችን ደህንነት በመጠበቅ የማር ምርታማነትን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ በንብ መንጋ ብዛትና በማር ምርት ከአፍሪካ አንደኛ መሆኗን ጠቅሰው ዘርፉ በዘመናዊ የማር አመራረት እየተለወጠ ነው ብለዋል።
የማር አመራረትን ለማዘመን በተሰጠው ትኩረት ባለፉት ዘጠኝ ወራት እንደ ሀገር 2 ነጥብ 2 ሚሊዮን ዘመናዊ ቀፎ መሰራጨቱንና 250ሺህ ቶን የማር ምርት መገኘቱን አመልክተዋል።
ኢትዮጵያ በእንስሳት ሀብቷና በተፈጥሮ በታደለችው የአየር ጸባይ ለማር ምርት ምቹ በመሆኗ ከዘርፉ የተሻለ ተጠቃሚ ለመሆን በትጋት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026