የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በኢትዮጵያ ሲሚንቶ የማምረት አቅምን በዓመት ወደ 20 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማድረስ ተችሏል - ሚኒስትር ሃብታሙ ተገኝ(ኢ/ር)

May 21, 2025

IDOPRESS

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሲሚንቶ የማምረት አቅምን በዓመት ወደ 20 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማድረስ መቻሉን የማዕድን ሚኒስትር ሃብታሙ ተገኝ(ኢ/ር) ገለጹ።

ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በድሬዳዋ ከተማ የተገነባውን የፓዮኔር ሲሚንቶ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ማስፋፊያ ፕሮጀክት መርቀዋል።

በዚሁ ወቅት የማዕድን ሚኒስትር ሃብታሙ ተገኝ(ኢ/ር) እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ሲሚንቶ የማምረት አቅምን በዓመት ወደ 20 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማድረስ መቻሉን ገልጸዋል።

ባለፉት ጥቂት ዓመታት ለሲሚንቶ ምርት አቅርቦትና ፍላጎት ምላሽ የሚሰጡ እንደ ለሚ ሲሚንቶ ዓይነት ግዙፍ ፋብሪካዎች ተገንብተው ስራ መጀመራቸውንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል።


ኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ መሰረተ ልማት የምትገነባ ሀገር በመሆኗ የሲሚንቶ ግብዓት ወሳኝ ነው ሲሉም ገልጸዋል።

አሁን ላይ የነባር ፋብሪካዎችን ምርታማነት በማሳደግና አዳዲሶችን ወደ ስራ በማስገባት ከሀገር ውስጥ በተጨማሪ ለጎረቤት ሀገራት ሲሚንቶ ማቅረብ የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ ነው ብለዋል።

በዚህም በኢትዮጵያ ሲሚንቶ የማምረት አቅምን በዓመት ወደ 20 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማድረስ መቻሉን ነው የገለጹት።

አራት የድንጋይ ከሰል ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን ወደ ስራ በማስገባት የሲሚንቶ አምራቾችን አቅም የማሳደግ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።


ለኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የግብዓት አቅርቦት ምላሽ ለመስጠት በብረት፣ እብነበረድ፣ ሲሚንቶና ሌሎች መስኮች ስኬታማ የምርታማነት አቅም እየተፈጠረ መሆኑንም ሚኒስትሩ አንስተዋል።

በኢትዮጵያ እና ቻይና ባለሃብቶች አጋርነት በአጭር ጊዜ የተገነባው የፓዮኔር ሲሚንቶ ፋብሪካም ከፍተኛ ጥራት ያለው ምርት በማምረት የኢትዮጵያ አዲስ የስራ ባህል ልምምድ መገለጫ ለመሆን መብቃቱን አስታውቀዋል።

ኢትዮጵያ በማዕድን ሃብት በዓይነትም ሆነ በብዛት ከፍተኛ አቅም ያላት መሆኗን ጠቁመው፤ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ማዕድን ከድህነት መውጫ አቅም እንዲሆን እየተሰራ ነው ብለዋል።


የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር በበኩላቸው፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ትኩረት የተሰጠው የተኪ ምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ ምርታማነትንና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።

በድሬዳዋ ከተማ የተገነባው ፓዮኔር ሲሚንቶ ፋብሪካ ከብክለት የጸዳ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ለስራ ዕድል ፈጠራና ለከተማዋ ኢኮኖሚ መነቃቃት ጉልህ ሚና መወጣት መጀመሩን አስረድተዋል።


የፓዮኔር ሲሚንቶ ፋብሪካ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ጄኔራል ማናጀር ሊዮን ዞን፥ ፋብሪካው ላለፉት 16 ዓመታት በኢትዮጵያ በስራ ላይ መቆየቱን አስታውሰው አሁን ላይ የማምረት አቅሙን በ600 ሺህ ቶን ማሳደጉን ተናግረዋል፡፡

ኩባንያው ከሲሚንቶ ማምረት ባሻገር ማህበራዊ ሃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝም ገልጸው፤ በዚህም በድሬዳዋ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ በንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና በመንገድ ስራ ላይ በስፋት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አብራርተዋል፡፡

ፋብሪካው አሁን ላይ ለ550 ሰራተኞች በቀጥታ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን በማህበራዊ ዘርፉም የዜጎችን ተጠቃሚነት ከፍ የሚያደርጉ የስራ ዕድሎችን መፍጠሩን ጠቅሰዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ሀዋሳን የቱሪዝም እና ኢንቨስትመንት ማዕከል የማድረግ ተግባራት ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...

Jun 14, 2026

በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ 72 ከመቶ የሚሆነው መሬት በዘር ተሸፍኗል

ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...

Jun 11, 2026

በዞኑ ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማር ምርት ተገኘ

ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...

Jun 4, 2026

በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችንና የኢንቨስትመንት እድሎችን ለማስተዋወቅ አስችሏል

ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...

May 25, 2026