
አዲስ አበባ፤ ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ ሲሚንቶ የማምረት አቅምን በዓመት ወደ 20 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማድረስ መቻሉን የማዕድን ሚኒስትር ሃብታሙ ተገኝ(ኢ/ር) ገለጹ።
ፕሬዝዳንት ታዬ አፅቀሥላሴ በድሬዳዋ ከተማ የተገነባውን የፓዮኔር ሲሚንቶ ማኑፋክቸሪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ማስፋፊያ ፕሮጀክት መርቀዋል።
በዚሁ ወቅት የማዕድን ሚኒስትር ሃብታሙ ተገኝ(ኢ/ር) እንደገለጹት፤ በኢትዮጵያ ሲሚንቶ የማምረት አቅምን በዓመት ወደ 20 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማድረስ መቻሉን ገልጸዋል።
ባለፉት ጥቂት ዓመታት ለሲሚንቶ ምርት አቅርቦትና ፍላጎት ምላሽ የሚሰጡ እንደ ለሚ ሲሚንቶ ዓይነት ግዙፍ ፋብሪካዎች ተገንብተው ስራ መጀመራቸውንም ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ ዘርፈ ብዙ መሰረተ ልማት የምትገነባ ሀገር በመሆኗ የሲሚንቶ ግብዓት ወሳኝ ነው ሲሉም ገልጸዋል።
አሁን ላይ የነባር ፋብሪካዎችን ምርታማነት በማሳደግና አዳዲሶችን ወደ ስራ በማስገባት ከሀገር ውስጥ በተጨማሪ ለጎረቤት ሀገራት ሲሚንቶ ማቅረብ የሚያስችል አቅም እየተፈጠረ ነው ብለዋል።
በዚህም በኢትዮጵያ ሲሚንቶ የማምረት አቅምን በዓመት ወደ 20 ሚሊዮን ሜትሪክ ቶን ማድረስ መቻሉን ነው የገለጹት።
አራት የድንጋይ ከሰል ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎችን ወደ ስራ በማስገባት የሲሚንቶ አምራቾችን አቅም የማሳደግ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም ተናግረዋል።

ለኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ የግብዓት አቅርቦት ምላሽ ለመስጠት በብረት፣ እብነበረድ፣ ሲሚንቶና ሌሎች መስኮች ስኬታማ የምርታማነት አቅም እየተፈጠረ መሆኑንም ሚኒስትሩ አንስተዋል።
በኢትዮጵያ እና ቻይና ባለሃብቶች አጋርነት በአጭር ጊዜ የተገነባው የፓዮኔር ሲሚንቶ ፋብሪካም ከፍተኛ ጥራት ያለው ምርት በማምረት የኢትዮጵያ አዲስ የስራ ባህል ልምምድ መገለጫ ለመሆን መብቃቱን አስታውቀዋል።
ኢትዮጵያ በማዕድን ሃብት በዓይነትም ሆነ በብዛት ከፍተኛ አቅም ያላት መሆኗን ጠቁመው፤ ከሀገራዊ ለውጡ ወዲህ ማዕድን ከድህነት መውጫ አቅም እንዲሆን እየተሰራ ነው ብለዋል።

የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሀር በበኩላቸው፤ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ትኩረት የተሰጠው የተኪ ምርት ንቅናቄ የኢንዱስትሪ ምርታማነትንና የውጭ ኢንቨስትመንትን ለማሳደግ ጉልህ ሚና እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።
በድሬዳዋ ከተማ የተገነባው ፓዮኔር ሲሚንቶ ፋብሪካ ከብክለት የጸዳ ቴክኖሎጂን በመጠቀም ለስራ ዕድል ፈጠራና ለከተማዋ ኢኮኖሚ መነቃቃት ጉልህ ሚና መወጣት መጀመሩን አስረድተዋል።

የፓዮኔር ሲሚንቶ ፋብሪካ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ጄኔራል ማናጀር ሊዮን ዞን፥ ፋብሪካው ላለፉት 16 ዓመታት በኢትዮጵያ በስራ ላይ መቆየቱን አስታውሰው አሁን ላይ የማምረት አቅሙን በ600 ሺህ ቶን ማሳደጉን ተናግረዋል፡፡
ኩባንያው ከሲሚንቶ ማምረት ባሻገር ማህበራዊ ሃላፊነቱን እየተወጣ እንደሚገኝም ገልጸው፤ በዚህም በድሬዳዋ በአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ በንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትና በመንገድ ስራ ላይ በስፋት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አብራርተዋል፡፡
ፋብሪካው አሁን ላይ ለ550 ሰራተኞች በቀጥታ የስራ ዕድል የፈጠረ ሲሆን በማህበራዊ ዘርፉም የዜጎችን ተጠቃሚነት ከፍ የሚያደርጉ የስራ ዕድሎችን መፍጠሩን ጠቅሰዋል፡፡
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026