
ጅማ፤ ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦ የእንስሳትና ሰብል ምርታማነትን ይበልጥ በማሳደግ የምግብ ዋስትናን ለማጎልበት በትኩረት እየተሰራ መሆኑን በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ሃላፊ እና የብልፅግና ፓርቲ ምክትል ፕሬዝዳንት አደም ፋራህ ገለጹ።
የንቦች ቀን እየተከበረ ሲሆን በዚህም በጅማ ዞን ማና ወረዳ የዘመናዊ ቀፎ የማር ክላስተር ተጎብኝቷል።

አቶ አደም በጉብኝቱ ወቅት እንዳመለከቱት፤ ግብርናውን አጠናክረን ከውጭ የሚገባን ምርት በሀገር ውስጥ ለመተካት ውጤታማ ስራ እየተከናወነ ነው።
በግብርናው ዘርፍ ብዛት እና ጥራት ያለውን ምርት ይበልጥ በማሳደግ የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።
ኢትዮጵያ መልክዓ ምድሯ እና የአየር ጸባይዋ ለማር ምርት የተመቸ በመሆኑ ማርን በብዛትና በጥራት በማምረት ለውጭ ገበያ የማቅረቡ ስራ መጠናከር ያለበት ነው ብለዋል።
የማር ምርትን በጥራት አዘጋጅቶ ወደ ውጭ የመላክና የገበያ ትስስር መፍጠር ለሀገር ከፍተኛ የገቢ ምንጭ በመሆኑ በዚህ በኩል ጥሩ ስራ እየተሰራ መሆኑንም ገልጸዋል።
የሌማት ትሩፋት አንዱና ዋነኛው ዓላማ የተሟላ የአመጋገብ ስርዓት ማምጣት ሲሆን በቀላሉ በጓሮ በሚለሙ የምግብ ዓይነቶች በመተግበር በማር፣ በወተት፣ በዶሮ ማርባት እና በእንቁላል እየተተገበረ መሆኑን ተናግረዋል።
ከማር ምርት በተጨማሪ በመስኖ ስንዴ ምርት፣ በሩዝ እና በፍራፍሬ ልማት የተጀመሩ ስራዎች ውጤታማ መሆናቸውን ገልጸዋል።
መንግስት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ የሚያደርግ የግብርና ልማትን የሚያበረታታ በመሆኑ በየደረጃው ያሉ አካላት ለግብርናው ምርታማነት በትኩረት መስራት አለባቸው ብለዋል።

በጉብኝቱ የተሳተፉት በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የምግብና የእርሻ ድርጅት የአፍሪካ ተወካይ ዳይሬክተር ጀነራል አበበ ሀይለገብርኤል በበኩላቸው፤ የንቦች ቀን መከበሩ ለንቦች እና ለአካባቢ ጥበቃ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ ያደርጋል ነው ያሉት።
ንቦች የማር ምርት ከመስጠት ያለፈ ሚና ያላቸው በመሆኑ ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለደን እንክብካቤና ለአረንጓዴ ልማት መነቃቃት ይፈጥራል ነው ያሉት።
በጅማ ዞን ማና ወረዳ በተደረገው ጉብኝትም የተመለከቱት የዘመናዊ ቀፎ የማር ልማት የሚበረታታ እና መስፋት ያለበት ተሞክሮ ሆኖ እንዳገኙት ጠቅሰዋል።
በጉብኝቱ ከዘመናዊ ቀፎ የማር ምርት በተጨማሪ የአቮካዶና የሙዝ ተክሎች ልማትም የተጎበኙ ሲሆን የአካባቢው አስተዳደርና የዘርፉ ባለሙያዎችም ተገኝተዋል።
ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...
Aug 27, 2026
ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...
Aug 14, 2026
ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...
Aug 13, 2026
ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...
Jul 31, 2026