
ጋምቤላ፤ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተለያዩ ዘርፎች የተገኙ ስኬቶችን በማስፋት የህዝብን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ ተግቶ መስራት እንደሚገባ ተመላከተ።
የክልሉ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን የዘጠኝ ወራት የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈፃጸም ገምግመዋል።
በምክር ቤቱ የሰው ሃብት፣የማህበራዊ ልማትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጋትሉዋክ ጋች እንደገለጹት፥ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በትምህርት ለትውልድ፣ በተማሪዎች ምገባና በሌሎች የትምህርት ልማት ስራዎች አበረታች ተግባራት ተከናውነዋል።
በቀጣይም ክልላዊና ሀገራዊ ፈተናዎች የሚሰጡበት ወቅት በመሆኑ የትምህርት ሴክተሩ ጥራትን ለማረጋገጥና የክልሉ ተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል ሲያከናውናቸው የነበሩ ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
በጤናው ዘርፍም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ድንገተኛና ተላላፊ በሽታዎችን በመከላከሉ ረገድ ስኬታማ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመው፥ በቀጣይም የክረምቱን መግቢያ ተከትሎ የወባ በሽታ እንዳይስፋፋ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።
የምክር ቤቱ የግብርና፣የመስኖና ቆላማ አካባቢ እና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዳዊት ድርኪያ በዘጠኝ ወራቱ የመስኖ መሰረተ ልማቶችን በማስፋት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ የተከናወኑ ስራዎች አበረታች ናቸው ብለዋል።
በአንፃሩ የግብርና ልማት ጣቢያ ሰራተኞች በስራ ገበታ ላይ ያለመገኘትና በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ረገድ ክፍተቶች መታየታቸውን ጠቁመው፥ በቀጣይ በተጠቀሱት ውስንነቶች ዙሪያ በትኩረት እንዲሰራ አሳስበዋል።
እንዲሁም በቀጣይ የመኸር ግብርናና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ስራዎች የሚከናወኑበት ጊዜ በመሆኑ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ወደ አርሶና አርብቶ አደሩ ዘልቀው በመግባት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።
በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ዘላቂ ሰላምና የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ በኩል ስኬታማ ስራዎች መከናወናቸውን የገለጹት ደግሞ የምክር ቤቱ የህግ፣ የፍትህና የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ኡፓራ አጉዋ ናቸው።
በቀጣይ የተገኘውን ሰላም በማጽናት የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለማፋጠን በትኩረት መስራት እንደሚገባም አቶ ኡፓራ ተናግረዋል።
የክልሉ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ከትናንት ጀምሮ ለሁለት ቀናት ሲያካሄድ የቆየው የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ማምሻውን ተጠናቋል።
ሀዋሳ፤ ሰኔ 6/2018(ኢዜአ)፦ ሀዋሳ ከተማን በማልማት የቱሪዝምና የኢንቨስትመንት ማዕከልነቷን ይበልጥ ለማሳደግ የሚከናወኑ የልማት ተግባራት ተጠናክረው እንደሚ...
Jun 14, 2026
ጋምቤላ፤ ሰኔ 3/2018(ኢዜአ)፦ በጋምቤላ ክልል በዘንድሮው የመኸር እርሻ ለማልማት ከታቀደው ውስጥ ከ72 በመቶ በላይ የሚሆነው መሬት በዘር መሸፈኑን የክልሉ ...
Jun 11, 2026
ደብረ ማርቆስ ፤ግንቦት 26/2018 (ኢዜአ)፦ በምስራቅ ጎጃም ዞን ከሰብል ልማት ጎን ለጎን በተከናወነ የንብ ማነብ ስራ ወደ 3 ሚሊዮን ኪሎ ግራም የሚጠጋ የማ...
Jun 4, 2026
ዲላ፤ ግንቦት 16/2018 (ኢዜአ)፡-ከ40 በላይ የንግድ ተቋማትና አጋር አካላት ተሳትፈውበት በዲላ ከተማ የተዘጋጀው "ቡኖ - ማላ" ኤክስፖ ምርቶችን እና የኢ...
May 25, 2026