የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ማህበረሰብ እና ባህል

በክልሉ የተገኙ ስኬቶችን በማስፋት የህዝብን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ መስራት ይገባል

May 21, 2025

IDOPRESS

ጋምቤላ፤ግንቦት 12/2017(ኢዜአ)፦በጋምቤላ ክልል ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተለያዩ ዘርፎች የተገኙ ስኬቶችን በማስፋት የህዝብን ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ ተግቶ መስራት እንደሚገባ ተመላከተ።


የክልሉ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴዎች የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶችን የዘጠኝ ወራት የልማትና የመልካም አስተዳደር እቅድ አፈፃጸም ገምግመዋል።


በምክር ቤቱ የሰው ሃብት፣የማህበራዊ ልማትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ጋትሉዋክ ጋች እንደገለጹት፥ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በትምህርት ለትውልድ፣ በተማሪዎች ምገባና በሌሎች የትምህርት ልማት ስራዎች አበረታች ተግባራት ተከናውነዋል።


በቀጣይም ክልላዊና ሀገራዊ ፈተናዎች የሚሰጡበት ወቅት በመሆኑ የትምህርት ሴክተሩ ጥራትን ለማረጋገጥና የክልሉ ተማሪዎች ውጤት እንዲሻሻል ሲያከናውናቸው የነበሩ ስራዎችን አጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።


በጤናው ዘርፍም ባለፉት ዘጠኝ ወራት ድንገተኛና ተላላፊ በሽታዎችን በመከላከሉ ረገድ ስኬታማ ስራዎች መሰራታቸውን ጠቁመው፥ በቀጣይም የክረምቱን መግቢያ ተከትሎ የወባ በሽታ እንዳይስፋፋ በትኩረት ሊሰራ ይገባል ብለዋል።


የምክር ቤቱ የግብርና፣የመስኖና ቆላማ አካባቢ እና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ዳዊት ድርኪያ በዘጠኝ ወራቱ የመስኖ መሰረተ ልማቶችን በማስፋት አርሶ አደሩን ተጠቃሚ ለማድረግ የተከናወኑ ስራዎች አበረታች ናቸው ብለዋል።


በአንፃሩ የግብርና ልማት ጣቢያ ሰራተኞች በስራ ገበታ ላይ ያለመገኘትና በነዳጅ አቅርቦትና ስርጭት ረገድ ክፍተቶች መታየታቸውን ጠቁመው፥ በቀጣይ በተጠቀሱት ውስንነቶች ዙሪያ በትኩረት እንዲሰራ አሳስበዋል።


እንዲሁም በቀጣይ የመኸር ግብርናና የተፈጥሮ ሀብት ልማት ስራዎች የሚከናወኑበት ጊዜ በመሆኑ የዘርፉ ባለድርሻ አካላት ወደ አርሶና አርብቶ አደሩ ዘልቀው በመግባት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።


በክልሉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ዘላቂ ሰላምና የህግ የበላይነትን በማረጋገጥ በኩል ስኬታማ ስራዎች መከናወናቸውን የገለጹት ደግሞ የምክር ቤቱ የህግ፣ የፍትህና የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ኡፓራ አጉዋ ናቸው።


በቀጣይ የተገኘውን ሰላም በማጽናት የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ስራዎችን ለማፋጠን በትኩረት መስራት እንደሚገባም አቶ ኡፓራ ተናግረዋል።


የክልሉ ምክር ቤት ቋሚ ኮሚቴ ከትናንት ጀምሮ ለሁለት ቀናት ሲያካሄድ የቆየው የአስፈፃሚ መስሪያ ቤቶች የዘጠኝ ወራት እቅድ አፈፃፀም ግምገማ ማምሻውን ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በሀዋሳ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው-ርዕሰ መስተዳድር ደስታ ሌዳሞ

ሀዋሳ፣ ነሐሴ20/2018 (ኢዜአ)፡-በሀዋሳ ከተማ የተጀመሩ የሐይቅ ዳርቻ እና የኮሪደር ልማት ሥራዎችን በተያዘላቸው ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ...

Aug 27, 2026

በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12  ባለሀብቶች ላይ  እርምጃ ተወሰደ

ሐረሪ ፤ነሐሴ 7/2018 (ኢዜአ)፦በሐረሪ ክልል የኢንቨስትመንት ፍቃድ እና መሬት ወስደው ወደ ግንባታና ማምረት ባልገቡ 12 ባለሀብቶች ላይ የኢንቨስትመንት...

Aug 14, 2026

በአማራ ክልል ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር ተሰጠ

ደሴ፤ነሐሴ 6/2018(ኢዜአ)፡-በአማራ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ173 ሺህ ለሚበልጡ አርሶ አደሮች የሁለተኛ ደረጃ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ደብተር መሰጠ...

Aug 13, 2026

በክልሉ በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል 

ባሕር ዳር ፤ ሐምሌ 23/2018(ኢዜአ)፦በአማራ ክልል በሁሉም ዘርፎች በተከናወኑ ተግባራት የተሻለ የኢኮኖሚ እድገት ማስመዝገብ መቻሉን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር...

Jul 31, 2026